የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

አገልግሎቱ የውጭ ባለሀብቶች በሚሰማሩባቸው የትኛውም የሥራ መስኮች አስተማማኝ የፀጥታና ደኅንነት ምህዳር እንዲፈጠር የሚያግዝ ስምሪት እያከናወነ ይገኛል

Jul 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የውጭ ባለሀብቶች በሚሰማሩባቸው የትኛውም የሥራ መስኮች አስተማማኝ የፀጥታና ደኅንነት ምህዳር እንዲፈጠር የሚያግዝ ስምሪት እያከናወነ እንደሚገኝ የአገልግሎቱ ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ሲሳይ ቶላ (ዶ/ር) አስታወቁ።

የአሜሪካ መንግሥት የመካከለኛው ምሥራቅ እና አፍሪካ ምክትል ረዳት ሚኒስትር ማርክ ሚቸል ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ስትራቴጂክ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመሥራት ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መረጃ እንዳመለከተው፤ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ሲሳይ ቶላ (ዶ/ር) የአሜሪካ መንግሥት የመካከለኛው ምሥራቅ እና አፍሪካ ምክትል ረዳት ሚኒስትር ማርክ ሚቸል ከተመራ ልዑክ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ሲሳይ ቶላ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት፤ ተቋሙ በኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት፣ ለንግድና ለሌሎችም የውጭ ባለሀብቶች ለሚሰማሩባቸው የትኛውም የሥራ መስኮች አስተማማኝ የፀጥታና ደኅንነት ምህዳር እንዲፈጠር የሚያግዝ ስምሪት እያከናወነ ይገኛል፡፡

ይህም ለአሜሪካ የቢዝነስ ማኅበረሰብ መተማመን የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በየጊዜው ሲያጋጥሙ የነበሩ የፀጥታ ስጋቶችን በማስወገድ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ደኅንነትንና ሰላምን የማረጋገጥ ሰፊ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥትም ቀጣናዊ መረጋጋት ለማስፈን የጋራ ተጠቃሚነትን መርህ ያደረጉ ስትራቴጂዎች በመንደፍና ቁርጠኛ አቋም በመያዝ እየተገበረ መሆኑን ገልጸው፤ የመረጃና ደኅንነት ተቋሙም በዚህ በኩል ያለውን ዝግጁነት ጠቁመዋል፡፡

የአሜሪካ መንግሥት የመካከለኛው ምሥራቅ እና አፍሪካ ምክትል ረዳት ሚኒስትር ማርክ ሚቸል በበኩላቸው፤ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ስትራቴጂክ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመሥራት ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል፡፡

ረዳት ሚኒስትር ማርክ ሚቸል የአሜሪካ ኩባንያዎች በሀገሪቱ በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች ተሰማርተው መስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ማብራሪያ እንደሰጡና ለዚህም አስቻይ ሁኔታዎች መኖሩን እንደገለፁ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢዜአ የላከው መረጃ አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉራጌ ዞን በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም  ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...

Jul 29, 2026

አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን ማጎልበት አለባት

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...

Jul 29, 2026

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...

Jul 16, 2026

የሩዝ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል

መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...

Jul 10, 2026