የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በሲዳማ ክልል በመኸር እርሻ ከ169 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይለማል 

Aug 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ ሐምሌ 25/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል በተያዘው የመኸር እርሻ ከ169 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአዝርዕት፣ በጥራጥሬና በስራስር ሰብሎች እንደሚለማ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ እንደገለጹት፤ በሲዳማ ክልል በተያዘው የመኸር እርሻ ከ169 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአዝርዕት፣ በጥራጥሬና በስራስር ሰብሎች ይለማል።

ኃላፊው አክለውም መኸር አብቃይ ለሆኑ ወረዳዎች 183 ሺህ 410 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያና 47 ሺህ 458 ኩንታል ምርጥ ዘር መሰራጨቱን ገልጸዋል።

ዘንድሮ በዘር ከሚሸፈነው ማሳ በጥራጥሬ፣ በብርዕና በሌሎች ዋና ዋና ሰብሎች 123 ሺህ ሄክታር መሬት እንደሚለማና ቀሪው በድንች፣ በስኳር ድንችና ሌሎች የስራ ስር ሰብሎች እንደሚለማ ገልጸዋል።

አርሶ አደሩ ማሳውን ለዘር እያዘጋጀ እንደሚገኝና በአንዳንድ ወረዳዎች የዘር መዝራት ስራ እንደተጀመረ ጠቁመዋል።

በበልግ እርሻ በዝናብ መቆራረጥ ምክንያት የጠፋ ሰብልን ለማካካስ ዘር እንደቀረበላቸውና በመኸር እርሻ ፈጥነው የሚደርሱ ሰብሎችን እንዲያለሙ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።


በክልሉ የደራራ ወረዳ አርሶ አደር ተሰማ ተስፋዬ፣ በበልግ ወቅት በበቆሎ ያለማነውን የደረሰ ሰብል በማንሳት ለመኸር እርሻ ቦሎቄና የስራ ስር ሰብል ለማልማት ዝግጅት እያደረግን ነው ብለዋል።

ፈጥነው የሚደርሱ ሰብሎች ዘር እንደቀረበላቸውና የግብርና ባለሙያዎች በቅርበት እገዛ እያደረጉላቸው መሆኑንም አርሶ አደሩ ገልጸዋል።

አርሶ አደር ታዲዮስ መልካሙ በበኩላቸው በግብርና ባለሙያዎች ድጋፍ በመታገዝ በመኸር የሚያለሙትን ማሳ እያዘጋጁ እንደሚገኙ ተናግረዋል።


በበልግ እርሻ በቆሎ በኩታ ገጠም እንዳለሙ ያነሱት አርሶ አደሩ የመኸሩንም በዚሁ የእርሻ ስነ-ዘዴ እንደሚያለሙም ገልጸዋል።

በክልሉ በመኸር እርሻ ከ430 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እንደሚሳተፉና ከሚለማው 169 ሺህ ሄክታር ማሳ ከ15 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚሰበሰብ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉራጌ ዞን በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም  ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...

Jul 29, 2026

አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን ማጎልበት አለባት

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...

Jul 29, 2026

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...

Jul 16, 2026

የሩዝ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል

መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...

Jul 10, 2026