የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአማራ ክልል የፍራፍሬ ልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

Aug 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል እየተካሄደ የሚገኘው የፍራፍሬ ልማት የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ደረጀ ማንደፍሮ ገለፁ።

የአማራ ክልል፣ የዞንና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች በቃሉ ወረዳ በክላስተር የለማ ፍራፍሬ ልማት ጎብኝተዋል።


የቢሮ ኃላፊው አቶ ደረጀ ማንደፍሮ እንደገለፁት፣ ክልሉ ለፍራፍሬ ልማት ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ይገኛል።

ባለፉት ሰባት ዓመታትም ቡናና አቮካዶን ጨምሮ ሌሎች የፍራፍሬ አይነቶች በመመረታቸው ከፍጆታ አልፎ ለውጭ ገበያ ጭምር ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል።

በክልሉ በአሁኑ ወቅት አርሶ አደሩን በማደራጀት በኩታ ገጠም የፍራፍሬ ልማት እንዲሳተፍና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል።


በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም 37 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ከ26 ሚሊዮን በላይ የቡናና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች እየተተከሉ መሆኑን ገልጸዋል።

በቃሉ ወረዳ በኩታ ገጠም የለማው የፍራፍሬ ችግኝም ተስፋ ሰጭና ለሌሎች አካባቢዎች ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል።

የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አህመድ ጋሎ በበኩላቸው፣ ዞኑ ለፍራፍሬ ልማት ያለውን ምቹነት በመጠቀም የአርሶ አደሩን ገቢ ማሳደግና ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።


አርሶ አደሩን በማደራጀት በኩታ ገጠም ማንጎ፣ ፓፓያ፣ ብርቱካን፣ አቮካዶና ሌሎች ፍራፍሬዎችን በማልማት ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።

በዘንድሮው አረንጓዴ አሻራም ሶስት ሺህ 700 ሄክታር መሬት በፍራፍሬ ችግኝ እየተሸፈነ እንደሚገኝ ጠቁመው አሁን ላይ መስኖን በመጠቀም በበጋ ጭምር የፍራፍሬ ችግኞችን መትከል መቻሉን ተናግረዋል።

አርሶ አደሩ የፍራፍሬን ጥቅም በተግባር በማየቱ በኩታ ገጠም እየተደራጀ ማልማት ጀምሯል ያሉት ደግሞ የቃሉ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን አህመድ ናቸው።


በዚህም በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጡና በሽታን የሚቋቋሙ ዝርያዎችም በመንግስት እየቀረቡላቸው ነው ብለዋል።

በቃሉ ወረዳ የ033 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ሙባረክ መሀመድ እንደገለጹት ፣ ፍራፍሬን በክላስተር ማልማት መቻላቸው ተጠቃሚ አድርጓቸዋል።

ባለፉት ጥቂት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተከሉዋቸው የማንጎና ሙዝ ችግኞች ለገበያ በማቅረብ በዘንድሮ ዓመት ብቻ ከ70 ሺህ ብር በላይ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።


በዘንድሮው ክረምትም ተጨማሪ 200 የማንጎ ችግኞችን መትከላቸውን ተናግረዋል።

በጉብኝቱ የክልል፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎችና አባላትን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉራጌ ዞን በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም  ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...

Jul 29, 2026

አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን ማጎልበት አለባት

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...

Jul 29, 2026

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...

Jul 16, 2026

የሩዝ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል

መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...

Jul 10, 2026