🔇Unmute
ባህር ዳር፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፦ በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው አስታወቁ።
«አርቆ ማየት፤ አልቆ መሥራት» በሚል መሪ ሐሳብ የመንግሥትና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ ትውውቅ መድረክ መካሄድ ጀምሯል።

ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው በዚሁ መድረክ እንደገለጹት፤ በከተማዋ የፀጥታ አካላትና በሕዝቡ ጠንካራ ቅንጅት አስተማማኝ ሰላምን ማስፈን ተችሏል።
ባህር ዳርን ውብ፣ ጽዱ እና አረንጓዴ የማድረግ ተግባር በተጨባጭ እውን ማድረግ መቻሉንና የመሠረተ ልማት ግንባታዎች የከተማዋን ገጽታ በከፍተኛ ደረጃ መቀየራቸውን ገልጸዋል።
የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶችም አዲስ የሥራ ባህል ተፈጥሮባቸው በአጭር ጊዜና በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ መደረጉንም አንስተዋል።
በከተማዋ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ቀልጣፋ እና ፍትሐዊ አገልግሎት በመስጠት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ የተቻለ ሲሆን ከ75 ሺህ በላይ ነዋሪዎች አገልግሎቱን እንዲያገኙ መደረጉን ጠቁመዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞላ ሁሴን በበኩላቸው፤ በከተማዋ ከጊዜ ወደ ጊዜ አስተማማኝ ሰላም እየሰፈነ መምጣቱን ገልጸዋል።
የተገኘው ሰላም ለማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማቶች መሳካት ቁልፍ መሠረት በመሆኑ ቀጣይነት እንዲኖረው ሁለንተናዊ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የታዩ ክፍተቶችን በማረም በአዲሱ በጀት ዓመት የላቀ ውጤት ለማስመዝገብና ከተማዋን ይበልጥ ለማልማት ሁሉም በቅንጅት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።
ባህር ዳር፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፦ በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል...
Sep 15, 2026
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026