የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የዓባይ ወንዝና የቀይ ባሕር ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ጉዳይ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበር ማዕከላዊ አጀንዳዎች ናቸው 

Sep 18, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ መስከረም 7/2019 (ኢዜአ)፦የዓባይ ወንዝ ፍትሐዊ የውሃ ሀብት ተጠቃሚነትና የባሕር በር ባለቤትነትን የማረጋገጥ ጉዳይ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበር ማዕከላዊ ስትራቴጂክ አጀንዳዎች መሆናቸውን ምሁራን ገለጹ።

የአዲስ አበባ አመራር አካዳሚ የዓባይ ወንዝና የባሕር በር ጉዳዮችን በተመለከተ የፓናል ውይይት አካሂዷል።

የማኅበራዊ ሳይንስ ምሁሩ ብርሃኑ ሌንጂሶ (ዶ/ር) በፓናሉ ላይ እንዳሉት፣ የዓባይና የባሕር በር ጉዳዮች በጂኦፖለቲካዊና በልማታዊ ትስስራቸው ተነጣጥለው ሊታዩ አይገባም።


የዓባይ ወንዝ ጉዳይ የልማት፣ የኢኮኖሚና የቀጣናዊ ትብብር ማዕከል በመሆኑ በጋራ ጥቅም ላይ የተመሠረተ አቀራረብ ሊከተል እንደሚገባ አመልክተዋል።

ሁለቱን ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች በተቀናጀ የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይና የልማት ስትራቴጂ መሠረት መምራት እንደሚያስፈልግም አንስተዋል።

በዚህም የዓባይ ወንዝ ፍትሐዊ የውሃ ሀብት ተጠቃሚነትና የባሕር በር ባለቤትነትን የማረጋገጥ ጉዳይ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማስከበር ማዕከላዊ ስትራቴጂክ አጀንዳዎች መሆናቸውን አስገንዝበዋል።


የአዲስ አበባ አመራር አካዳሚ መሪ ተመራማሪ አቶ ሰለሞን ተፈራ በበኩላቸው፣ የባሕር በርና የዓባይ ጉዳዮች ተነጣጥለው ሳይሆን በአንድ ሀገራዊ ማዕቀፍ ውስጥ ተቀናጅተው ሊታዩ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ጉዳዮቹ በምሁራን ጥናትና በጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ሊመሩ እንደሚገባም ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፌዴራሊዝምና ገቨርናንስ መምህርና ተመራማሪ ተስፋዬ ጂማ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የባሕር በር ጉዳይ ከሉዓላዊነት፣ ከኢኮኖሚ ዕድገትና ቀጣናዊ ሰላም የተቆራኘ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ነው ብለዋል።


የሀገር ህልውናን፣ ደህንነትንና የዜጎችን ማኅበራዊ ልማት ከሚያሳድጉ ጉዳዮች አኳያ፣ የባሕር በርና የዓባይ ወንዝ ጉዳዮች በአንድ ማዕቀፍ ውስጥ ሊታዩ እንደሚገባ አንስተዋል።

ምሁራን በጥናትና ምርምር የተደገፈ የፖሊሲ ግብዓት በማቅረብ፣ እንዲሁም የሕዝብ ግንዛቤን በማሳደግ፣ ሀገራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ በሚደረገው ሂደት አዎንታዊ ሚና ማበርከት እንደሚችሉም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በባህር ዳር ከተማ አስተማማኝ ሰላምና ተጨባጭ የልማት ስራዎችን ማከናወን ተችሏል

ባህር ዳር፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፦ በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል...

Sep 15, 2026

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026