የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ተቋማቱ ዲጂታል ኢትዮጵያ ሽግግርን ለማፋጠን በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መከሩ

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ታኀሣሥ 26/2017(ኢዜአ)፦ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና ኢትዮ ቴሌኮም የዲጂታል ኢትዮጵያ ሽግግርን ለማፋጠን በሚያስችሉ ተግባራት ላይ መከሩ።

የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር ) የኢትዮ ቴሌኮም ኤክስፒሪየንስ ማዕከልን የጎበኙ ሲሆን ከኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ጋር ተወያይተዋል።

ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ኢትዮ ቴሌኮም ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ግንባር ቀደም ሚና የሚጫወት ተቋም ነው ብለዋል።

ኩባንያው በዲጂታል አገልግሎቶች እና ቴሌብር አስደማሚ ውጤት በእያስመዘገበ ስለመሆኑም ገልጸዋል።


ዲጂታል አገልግሎት ተደራሽነትና አካታችነት በመጨመር ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በሚያስችሉ የኢጋቨርንመንት፣ ኢኮሜርስ፣ ኢኖቬሽን፣ በጀማሪ የሥራ ፈጠራ፣ ጥናትና ምርምር፣ ስማርት ስልክ ስርጸት እና የዲጂታል ክህሎትን ለመሻሻል በቅንጅት እንሰራለን ብለዋል፡፡

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ኢትዮ ቴሌኮም የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ ለማሳካት ያከናወናቸውን በተለይም ገጠራማ አካባቢዎችን ጨምሮ ለዜጎች የዲጂታል መሠረተ ልማት ተደራሽ ለማድረግ እንዲሁም በቴሌብር ዲጂታል መፍትሔዎች፣ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶች እና ማኅበራዊ ኃላፊነት ስላከናወናቸው ተግባራት ገልጸዋል፡፡

የስማርት ሲቲ ፕሮጀክትን ጨምሮ እንደ ግብርና፣ ትምህርት፣ ጤና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ትራንስፖርት፣ ፋይናንስ እና ቱሪዝም ያሉ ዘርፎችን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል ግዙፍ አቅም መገንባቱንም አረጋግጠዋል፡፡

በመጨረሻም ተቋማቱ የዲጂታል ኢትዮጵያ ትራንስፎርሜሽን ለማፋጠን ቋሚ የጋራ መድረክ በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026