የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኢትዮጵያ በስታርታአፕ ዘርፍ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርጋትን ስነ-ምህዳር እየገነባች ነው

Mar 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በስታርታአፕ ዘርፍ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርጋትን ስነ-ምህዳር እየገነባች እንደምትገኝ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ገለጹ።


የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኮሪያ ዓለም ዓቀፍ ተራድኦ ድርጅት (ኮይካ) ጋር በመተባበር የስታርታፕ ዲጂታል አማራጭ ዲዛይን ምዕራፍ የተመለከተ አውደ ጥናት አካሄዷል።


በአውደ ጥናቱ ላይ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ፣ በኢትዮጵያ የኮሪያ ዓለም ዓቀፍ ተራድኦ ድርጅት ምክትል ዳይሬክተር ያንግሺን ፓርክ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።


ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የጀማሪ የስራ ፈጠራ (ስታርታፕ) ዘርፍ ከሀገር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ማድረግ የሚያስችል ምቹ ስነ-ምህዳር መፍጠርን ያለመ ነው።


የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የስታርታፕ መድረክ ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚያስችል ስነ-ምህዳር ለመገንባት እየሰራች እንደምትገኝ አመልክተዋል።


ስታርታፕ ፈጣን የሀገር ኢኮኖሚ ማበልፀጊያ ሞተር ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው የኢትዮጵያ ስታርታፕ ዲጂታል ፕላትፎርም ዘርፉን ለማሳደግ እና ኢኮኖሚውን የመደገፍ ፋይዳ አለው ብለዋል።


መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት ብዙ ሀብት ማፍራት የቻሉ ወጣቶች እና ዜጎች ተፈጥረዋል ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው።


በኢትዮጵያ የኮሪያ አለም ዓቀፍ ተራድኦ ድርጅት ምክትል ዳይሬክተር ያንግሺን ፓርክ (ካይካ) ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ በስታርታፕ ዘርፍ ላይ የምታደርገውን የስነ-ምህዳር ግንባታ ስኬታማ እንዲሆን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አመልክተዋል።


ኮይካ ኢትዮጵያ በዘርፉ ለምታከናውናቸው ስራዎች ድጋፍ እንደሚያደርግ መግለጻቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026