የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የግብይት ማዕከላትን ደረጃ የማሻሻል ሥራ እየተከናወነ ነው-ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ ጥር 14 /2018(ኢዜአ)፦ገበያን ለማረጋጋትና ህገወጥ ንግድን ለመቆጣጠር የሚረዱ የግብይት ማዕከላትን ከማስፋት ባለፈ ደረጃቸውን የማሻሻል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለፁ።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሚኒስቴሩ ገበያን ለማረጋጋትና ህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴን ለመቆጣጠር የሚረዱ የግብይት ማዕከላትን ከማስፋፋት ባለፈ ደረጃቸውን የማሻሻል ሥራ በመላ ሀገሪቱ እያከናወነ ይገኛል።


ቀደም ሲል ማህበረሰቡ በሚፈለገው ልክ የግብይት ማዕከላት ባለመስፋፋታቸው የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለመሸመት አስቻይ ሁኔታዎች እንዳልነበሩ አስታውሰዋል፡፡

የንግድ ስርዓቱን ለማዘመንና የግብይት ማዕከላትን ለማስፋፋት ትኩረት ተሰጥቷል


ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ችግሩን በመፍታት ገበያውን ለማረጋጋት በተሰራው ሥራ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ1ሺህ 900 በላይ የቅዳሜና እሁድ የግብይት ማዕከላትን ማቋቋም ስለመቻሉም ተናግረዋል፡፡

በንግድ ሥርዓቱ ሲስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት የገበያ ማዕከላትን ከማስፋፋት ባለፈ ደረጃቸውን የማሻሻልና የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውንም ገልጸዋል።


የግብይት ማዕከላቱ ጤናማ የንግድ ስርዓትን ለማሳለጥና ገበያን ለማረጋጋት ሚናቸው የጎላ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ማዕከላቱን በመሰረተ ልማት የማጠናከር ሥራ መጀመሩንም ተናግረዋል።

ይህም በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ምርቶችን ለማህበረሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ ማስቻሉን አስረድተዋል።

ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ ህዝብን ለጉዳት ሲዳርጉ የነበሩ አካላትም በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ነው ሚኒስትሩ ያስታወቁት።

በተከናወኑ የቁጥጥርና መሰል ሥራዎች የዋጋ ግሽበቱን መቀነስ እንደተቻለ ጠቁመው ተግባሩን የማጠናከር ሥራ በልዩ ትኩረት እንደሚመራም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026