🔇Unmute
ወላይታ ሶዶ ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ልማት ባልገቡ ባለሀብቶች ላይ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑ ተገለጸ።
በክልሉ ኮንትሮባንድ እና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን በመከላከል ጤናማ የገበያ ሥርአት ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቷል
የክልሉ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር አፀደ አይዛ በነገው እለት የሚካሄደውን የኢንቨስትመንት ፎረም አስመልክተው ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጭ ለማቅረብ በመቻሉ በርካታ ባለሃብቶችን ለመሳብ እየተቻለ መሆኑን አብራርተዋል።
በተያዘው በጀት ዓመት 10 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 226 ፕሮጀክቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወሰደው ወደ ሥራ ገብተዋል ነው ያሉት።
ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ እየተካሔደ ያለው የድጋፍና የክትትል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ኮሚሽነሯ የገለጹት።
በአሁኑ ወቅትም ለኢንቨስትመንት መሬት ተረክበው ወደልማት ባልገቡ ባለሀብቶች ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በተለዩ 81 ፕሮጀክቶች ላይ ከማስጠንቀቂያ ጀምሮ አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃ የተወሰደ ሲሆን 13 ሺህ 600 ሄክታር መሬት ወደ መሬት ባንክ ለማስገባት መቻሉን አስታውቀዋል።
በነገው እለት የሚካሔደው የኢንቨስትመንት ፎረም ከባለሀብቶች ጋር ውይይቶችን በማድረግ በዘርፉ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያግዝ መሆኑን አመልክተዋል።
በመሆኑም ባለሀብቶች በክልሉ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጭ በመጠቀም በኢንዱስትሪ፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026