🔇Unmute
ጅግጅጋ፤ መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ በሶማሌ ክልል የነዳጅ ግብይትን ህጋዊነት በመቆጣጠር የትራንስፖርት እንቅስቃሴን ለማሳለጥ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ንግድና ትራንስፖርት ቢሮ ገለጸ።
የሶማሌ ክልል ንግድና ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዱልሀኪም ሼክ ሀሰን በሰጡት መግለጫ በመካካለኛው ምስራቅ የተከሰተውን አለመረጋጋት ተከትሎ የገጠመው የነዳጅ ግብይትና አቅርቦት ጫና በህብረተሰቡ ላይ ተጽዕኖ እንዳያደርስ ጥብቅ ቁጥጥር መደረጉን ገልጸዋል።
ለተግባራዊነቱም የቅድሚያ ቅድሚያ ነዳጅ ለሚያስፈልጋቸው ተሽከርካሪዎች፣ የኤክስፖርት ድርጅቶች፣ የመንግሥትና የግል ፕሮጀክቶች፣ የገቢና ወጪ ንግድን ጨምሮ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን የሚያጓጉዙ ተሽከርካሪዎች ተደራሽ መደረጉን አንስተዋል።
ከዚህ ባለፈም ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትን ለመቆጣጠር የክልሉ የጸጥታ ተቋማት ከፌዴራል ፖሊስና ከጉምሩክ ኮሚሽን ጋር በቅንጅት እየተሠራ ነው ብለዋል።
በዚህም ህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመግታት በተደረገው ጥረት 3ሺህ 500 ሊትር ነዳጅ ከሰሞኑ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጸዋል።
ህብረተሰቡ ህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመቆጣጠር በሚደረገው ቅንጅታዊ ስራ ያለውን ተሳትፎ እንዲያጠናክርም ሃላፊው ጠይቀዋል።
በክልሉ አዲሱ የነዳጅ ጭማሪ ታሪፍ መደረጉንና ህብረተሰቡ ነዳጅን በቁጠባ እንዲጠቀም የግንዛቤ ስራ እየተካሄደ መሆኑንም ጠቁመዋል።
ህብረተሰቡ ሌሎች ታዳሽ ሀይልን በመጠቀምና አላስፈላጊ ጉዞ በመቀነስ የነዳጅ ቁጠባውን ተግባራዊ እንዲያደርግም መክረዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026