የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለዲጂታል ኢትዮጵያ ግንባታ ያላቸውን ሚና ለማጠናከር ትኩረት ተሰጥቷል

Apr 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፦የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለዲጂታል ኢትዮጵያ ግንባታ ያላቸውን ሚና ለማጠናከር ትኩረት መሰጠቱን በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የትምህርትና ክህሎት ለሥራ (ኢዝ) ፕሮጀክት አስተባባሪ ገለጹ።

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የትምህርትና ክህሎት ለሥራ (ኢዝ) ፕሮጀክት ለ12 ክልሎች እና ሁለት ከተማ አስተዳደሮች የሥራና ክህሎት ቢሮዎች የአይ ሲ ቲ መሰረተ ልማት ድጋፎች አድርጓል።


ሚኒስቴሩ ድጋፍ ካደረጋቸው መካከል ኮምፒውተሮች፣ የኔትወርክ መሰረተ ልማት ቁሳቁሶች፣ ለቪዲዮ ኮንፍረንስ የሚያገለግሉ ቴሌቪዥኖች፣ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ጄኔሬተሮችና የሶላር ፓኔሎች ይገኙበታል።

በሚኒስቴሩ የኢዝ ፕሮጀክት አስተባባሪና የኢፌዴሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ሀፍቶም ገብረእግዚአብሄር እንዳሉት፤ የሥልጠና ማዕከላትን በዘመናዊ መንገድ በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ የመሰረተ ልማት ማሟላት ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል።

ለአብነትም ሚኒስቴሩ ከልማት አጋሮች ጋር በመተባበር 70 ኮሌጆች አስፈላጊው መሰረተ ልማት እንዲሟላላቸው መደረጉን ጠቁመው፤ በዚህም የሥልጠና አቅምን ከፍ ያደረጉ ውጤቶች እየተገኘበት ነው ብለዋል።

ዛሬ ፕሮጀክቱ ለ12ቱ ክልሎችና ለሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ድጋፍ ያደረገው የአይ ሲ ቲ መሰረተ ልማቶች ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን በማድረግ ሂደት ዓይነተኛ ሚና እንዳለውም አክለዋል።

ድጋፉ እንደ ሀገር ተግባራዊ በመደረግ ላይ ያለው የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና መርሃ ግብርን ስኬታማ ከማድረግ አኳያ ፋይዳ እንዳለውም አብራርተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ዳግማዊት ግርማ፤ ወጣቱ የዲጂታል ክህሎት አዳብሮ የርቀት ሥራዎች (ሪሞት ጆብስን) ጨምሮ አዳዲስ የሥራ ዕድሎች ተጠቃሚ እንዲሆን እየሰራን ነው ብለዋል።


የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶች መገኘታቸው ለሥራው መቃናት ትልቅ አበርክቶ እንዳለው ተናግረዋል።

የኦሮሚያ ክልል ሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ነስረዲን ቃዲ በበኩላቸው፤ በክልሉ ከመደበኛ ስልጠና ባሻገር የነዋሪዎችን የዲጂታል ክህሎት ለማሳደግ ያለመ ሕዝባዊ ስልጠና መርሃ ግብር ተጀምሯል ብለዋል።


ዛሬ የተገኘው ድጋፍ ሥራውን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመፈጸም ትልቅ ሚና ይጫወታል ብለዋል።


የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዓለሙ ገብሬ እንደገለጹት፤ ድጋፉ በክልሉ የሚገኙ የሥልጠና ማዕከላት ሥልጠናዎችን በጥራትና ዘመናዊ በሆነ መልኩ ተደራሽ እንዲያደርጉ ተጨማሪ አቅም ይፈጥራል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026