የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በተፈጠረልን የሥራ ዕድል የተሻለ ደረጃ ላይ ለመድረስ ተግተን እየሰራን ነው-የኮምቦልቻ ከተማ ወጣቶች

Apr 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ ሚያዚያ 7/2018 (ኢዜአ)፦በተፈጠረላቸው የሥራ ዕድል ከቤተሰብ ጥገኝነት በመላቀቅ ኑሯቸውን ለመቀየርና የተሻለ ደረጃ ላይ ለመድረስ ተግተው እየሰሩ መሆኑን በኮምቦልቻ ከተማ ወደሥራ የገቡ ወጣቶች ገለጹ።

የከተማ አስተዳደሩ ሥራና ክህሎት መምሪያ በበኩሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለ12 ሺህ 876 ሰዎች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን አስታውቋል።

የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው መካከል ወጣት መሀመድ ጌታቸው ለኢዜአ እንደገለጸው፣ ቀደም ሲል ሥራ በማጣቱ ምክንያት የቤተሰብ ጥገኛ ሆኖ ቆይቷል።


ዘንድሮ በከተማ አስተዳደሩ በተደረገለት የመስሪያ ቦታ ድጋፍ የሸቀጣሸቀጥ ሱቅ ከፍቶ የራሱን ሥራ መጀመሩን ገልጾ፣ በዚህም ከቤተሰብ ጥገኝነት በመላቀቅ ኑሮውን ለማሻሻል ጠንክሮ እየሰራ መሆኑን ተናግሯል።

ወጣት ካሱ ታረቀኝ በበኩሏ በተመቻቸላት የመስሪያ ቦታ በአገልግሎት ዘርፍ ተሰማርታ በምታገኘው ገቢ ከቤተሰብ ጠባቂነት ተላቃ ተጠቃሚ መሆን እንደጀመረች ተናግራለች።

"ያለሥራ ብዙ የከፋ ጊዜ አሳልፊያለው" የምትለው ወጣቷ ዘንድሮ ባገኘችው የሥራ ዕድል ጠንክራ በመስራት የተሻለ ደረጃ ላይ ለመድረስና ሀብት ለማፍራት ግብ ማስቀመጧን ተናግራለች።


ለዚህም በሥራዋ ውጤታማ ለመሆን ተግታ እየሰራች መሆኑን ጠቅሳ፣ ከተማ አስተዳደሩ በመስሪያ ቦታ ያደረገላት ድጋፍ በሥራዋ ውጤታማ እንድትሆን ጠቀሜታ አለው ብላለች።

የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ ይትባረክ ጌታሁን በበኩላቸው፣ በበጀት ዓመቱ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጥሮ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግና ዘርፉን ለማነቃቃት በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።


በየደረጃው ያለው አመራር ከዘርፉ ባለሙያ ጋር ተግባብቶ ወደሥራ በመግባቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለ12 ሺህ 876 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል ብለዋል።

በየአካባቢው ያሉ ፀጋዎችን በመለየት ወጣቶች ወደሥራ እንዲገቡ መደረጉን ገልጸው፣ ከተሰማሩባቸው የሥራ መስኮች መካከል ግብርና፣ አገልግሎት፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ንግድ፣ ኮንስትራክሽንና ማዕድን እንደሚገኙበት አመልክተዋል።

እንደ ኃላፊው ገለጻ ሥራ ለመጀመር የገንዘብ እጥረት ላለባቸው የሥራ ዕድል ተጠቃሚዎች ከ38 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር የተመቻቸ ሲሆን፣ በሥራቸው ስኬታማ እንዲሆኑም የገበያ ትስስር እየተፈጠረላቸው ተናግረዋል።

ግንባታቸው በተጠናቀቁ 12 ሼዶች የተደራጁ ወጣቶች ወደ ሥራ መግባታቸውን ገልጸው፣ በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራትም በሌሎች ዘርፎች የተሻለ የሥራ ዕድል ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።

በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር በተያዘው በጀት ዓመት ለ20 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ከአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026