የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ጥምረቱ ኢትዮጵያ የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን የምታከናውናቸውን ውጤታማ ተግባራት መደገፉን ይቀጥላል

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ምርታማነትን ለማረጋገጥ የምታከናውናቸው ውጤታማ ተግባራት መደገፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት (አግራ) ገለጸ።

የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት (አግራ-AGRA) ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች በሲዳማ ክልል የኤልቶ ገበሬዎች ህብረት ሥራ ዩኒየን የሥራ እንቅስቃሴን ዛሬ ጎብኝተዋል።

አግራ አነስተኛ ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮችን በግብዓትና በቴክኖሎጂ በመደገፍ ግብርናን ለማሳደግ እኤአ በ2006 የተመሰረተ አፍሪካ መር ተቋም ነው።

አግራ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ላይ አተኩሮ የሚሰራ ሲሆን የምርጥ ዘር አቅርቦት፣ የአፈር ለምነት ማስጠበቅ፣ የገበያ ትስስርን ማመቻቸትና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ግቦችን ለማሳካት እየተንቀሳቀሰ ያለ ጥምረት ነው።

የኢትዮጵያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጥምረቱ የቦርድ ሊቀ መንበር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት፤ ጥምረቱ ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ በ16 ሀገራት የግብርናውን ዘርፍ ውጤታማነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ድጋፍ ያደርጋል።


በተለይም በኢትዮጵያ አነስተኛ ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮች ምርታማነትን በማሳደግ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በተለያየ መንገድ እየደገፈ መሆኑንም አስታውቀዋል።

የጥምረቱ ፕሬዚዳንት አሊስ ሩህዌዛ በበኩላቸው ድርጅቱ በአፍሪካ የግብርና ስርዓት ሽግግርን ለማጠናከር በተለይም አነስተኛ ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየሰራ ነው ብለዋል።


አግራ አርሶ አደሮች ባላቸው አነስተኛ ማሳ ላይ አስፈላጊው ግብዓትና ቴክኖሎጂዎችን በማቅረብ ውጤታማ መሆን እንደሚችሉ ያምናል ያሉት ፕሬዚዳንቱ ይህም የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲፋጠን ያደርጋል፤ ውጤትም ታይቶበታል ብለዋል።

በአግራ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ይኼነው ዘውዴ (ዶ/ር) ጥምረቱ ምርጥ ዘርና ሌሎች ግብዓትን ከማሳለጥ ባሻገር የገበያ ትስስር እንዲፈጠር የማድረግ እንዲሁም ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ግብርናን ለማረጋገጥ የማገዝ ስራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።


በዚህም ከተለያዩ አካላት ጋር በትብብር የተከናወኑ ግብርናን የማዘመን፣ ምርታማነትን የማረጋገጥና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት የማሳደግ ጥረቶች ውጤት ማስመዝገባቸውን አንስተዋል።

የሲዳማ ኤልቶ የገበሬዎች የህብረት ሥራ ዩኒየን ሥራ አስኪያጅ አቶ ሲሳይ ዮሐንስ ጥምረቱ በፈጠረው የተቀናጀ ስራ አባላቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡


በተለይም የቴክኖሎጂ አቅርቦቱ የሚጠፋውን ጊዜና ጉልበት በማዳን፣ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያውን የማረጋጋት ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026