የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ከግብ ለማድረስ የኀብረት ሥራ ማህበራትና ዩኒየኖች ሚና የላቀ ነው

Apr 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ሚያዚያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የተጀመረውን የግብርና ትራንስፎርሜሽን ከግብ ለማድረስ የኀብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየኖችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አመለከተ።

የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን "ወደ ቀበሌ መድረስ" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጀው 2ኛው ሀገር አቀፍ የህብረት ስራ ሪፎርም የንቅናቄ መድረክ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እየተካሔደ ነው።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር እያሱ ኤልያስ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ ሀገሪቱ ግብርናን ዋነኛ የኢኮኖሚ ማእከል በማድረግ ወደ ኢንዱስትሪ ለመሸጋገር እየተጋች ትገኛለች።

ለዚህም ባለፉት የለውጥ ዓመታት በመንግሥት የግብርና ትራንስፎርሜሽን ተነድፎ በተደረገው ርብርብ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል።

ከተገኘው ውጤት ውስጥ አንድም መሬት ጦም እንዳያድር በሚል መርህ በየደረጃው በተደረገው ንቅናቄ በዓመት የሚለማውን መሬት ከ14 ሚሊዮን ወደ 22 ሚሊዮን ማሳደግ መቻሉን አውሰተዋል።

ከለውጡ በፊት 500 ሚሊዮን ኩንታል ብቻ የነበረው ዓመታዊ የሰብል ምርት ከሶስት እጥፍ በላይ ማሳደግ መቻሉንም አስረድተዋል።

በዚህም የተጀመረውን የግብርና ትራንስፎርሜሽን ትግበራ ከግብ ለማድረስ የኀብረት ሥራ ማህበራትና ዩኒየኖች ሚና የላቀ መሆኑንም አመልክተዋል።

ለዚሁ ስኬትም የኀብረት ስራ ማህበራትና ዩኒየኖች ማዳበሪያ፣ ምርጥ ዘር እና ሌሎች ግብዓቶችን በበቂ ሁኔታ በማቅረብ እያከናወኑት ያለውን ተግባር ሊያጠናክሩ ይገባል ብለዋል።

በግብርና ሚኒስቴር የግብዓትና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) በበኩላቸው ፤ ግብርናና ኀብረት ስራ ማህበራት ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ ያላቸው አበርክቶ ሰፊ መሆኑን ጠቁመዋል።

በተለይ ኀብረት ስራ ማህበራት በውጭ ግብይት ተሳትፎ፣ በብድርና ቁጠባ ረገድ ያላቸው አስተዋጽኦ እያደገ መምጣቱን ገልፀው፤ በግብርና ምርት ግብይት ረገድ የመሪነት ሚናቸውን በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባም አመልክተዋል።

ኮሚሽኑ ባዘጋጀውና ለተከታታይ ስምንት ቀናት በሚቆየው ሀገር አቀፍ የኀብረት ስራ የልማት አመቻች ባለሙያዎች ስልጠና ላይ ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ 4 ሺህ የቀበሌ አደራጅ ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026