የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኢትዮጵያ ለባለብዙ ወገን ዓለም አቀፍ የንግድ ስርዓት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ ናት

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ ኢትዮጵያ በሁሉን አቀፍ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ለሃገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች ለንግድና ኢንቨስትመንት ምቹ ከመሆን ባለፈ ለባለብዙ ወገን ዓለም አቀፍ የንግድ ስርዓት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆኗን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።


የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት 7ኛው የስራ ቡድን ስብሰባ በስዊዘርላንጅ ጄኔቫ በይፋ መካሄድ ጀምሯል።

ሚኒስትሩ በስብሰባው መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የኢትዮጵያን የአባልነት ጉዞ በማፋጠን ረገድ የስራ ቡድን ስብሰባ ሊቀመንበር፣ ሴክሬታሪያትና አባላት ላደረጉት ያላሰለሰ ድጋፍና ንቁ ተሳትፎ አመስግነዋል።

ባለፈው መስከረም ከተካሄደው 6ኛው የስራ ቡድን ስብሰባ ወዲህ ኢትዮጵያ በባለብዙ ወገንና በሁለትዮሽ ድርድሮች ከፍተኛ እመርታ አሳይታለች ብለዋል።

ለ226 የአባል ሃገራት ጥያቄዎች ጥልቅ ምላሾችን የመስጠት፣ የስራ ቡድን ረቂቅ ሪፖርትን የማዳበርና 32 የግዴታ አንቀጾችን የማጠናቀቅ ስራ መከናወኑንም በመድረኩ ላይ አብራርተዋል።


ከ9 አባላት ጋር የሁለትዮሽ የገበያ ዕድል ድርድሮችን አጠናቀናል ሲሉም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከአባላት የተነሱ ወሳኝ ቀሪ ጉዳዮችን በዳበረ ይዘትና ገንቢ አካሄድ ለማከናወን ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በሁሉን አቀፍ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ለሃገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች ለንግድና ኢንቨስትመንት ምቹ ከመሆን ባለፈ ለባለብዙ ወገን ዓለም አቀፍ የንግድ ስርዓት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆኗንም አረጋግጠዋል።

7ኛው የስራ ቡድን ስብሰባ ዛሬ ቀኑን ሙሉና ነገም ቀጥሎ የሚካሄድ መሆኑን ኢዜአ ከስፍራው ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026