የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር ዞን በመጭው የምርት ዘመን ከ412 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት በዘር ይሸፈናል

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ሚያዝያ 20/2018 (ኢዜአ)፡- በአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር ዞን በመጭው የመኸር ወቅት 412 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን እየተሠራ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በመምሪያው የሰብል ልማትና ጥበቃ ቡድን መሪ አንዱዓለም አያሌው ለኢዜአ እንዳሉት፤ ለመጭው የመኸር ወቅት 412 ሺህ 480 ሔክታር መሬት በዘር በመሸፈን ከ17 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ እየተሠራ ነው።


ከዚህ ውስጥም 70 በመቶው በኩታ ገጠም የሚለማ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅትም ከ85 ሺህ ሔክታር በላይ መሬት ለ2ኛ ጊዜ ደጋግሞ በማረስ ለዘር ዝግጁ ተደርጓል ብለዋል።

ከሚያስፈልገው 840 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ እስካሁን ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነውን በማስገባት ለአርሶ አደሩ እየተሰራጨ መሆኑን አረጋግጠዋል።

ከ5 ሺህ ኩንታል በላይ የበቆሎ ምርጥ ዘር ተሰራጨቷል ያሉት ቡድን መሪው፤ በመስመር መዝራትና ዘመናዊ ቴክኖሎጅዎችን መጠቀም ላይ በማተኮር እንደሚሰራም አስረድተዋል።

በየደረጃው ያለው የግብርና ባለሙያ እና አመራሩ አርሶ አደሩን በመደገፍና በማማከር የሚጠበቀውን የምርት እድገት ለማስመዝገብ በቁርጠኝነት እየሠራ መሆኑን ምአስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026