የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ ጥራትና ደህንነቱ የተረጋገጠ ከ169 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር እየተሰራጨ ነው 

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህርዳር ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ለ2018/19 የምርት ዘመን ጥራትና ደህንነቱ የተረጋገጠ ከ169 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ እየተሰራጨ መሆኑን የክልሉ የግብርና ጥራትና ደህንነት ባለስልጣን አስታወቀ።

‎የባለስልጣኑ ምክትል ኃላፊ አቶ ዘላለም ልየው ለኢዜአ እንደገለፁት፤ጥራትና ደህንነቱ በላብራቶሪ የተረጋገጠ ዘር ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግ የክልሉን ምርታማነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።


በዚህም ለ2018/2019 የምርት ዘመን ጥቅም ላይ የሚውል ከ169 ሺህ ኩንታል በላይ የበቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ፣ ጤፍና ሌሎች የሰብል ዘር ጥራትና ደህንነት በላብራቶሪ በማረጋገጥ እየተሰራጨ መሆኑን ገልጸዋል።

የዘር ጥራትና ቁጥጥር ስራው የተካሄደው በአማራ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ፣ በግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን፣ በዩኒየኖችና በግል ዘር አብዢዎች የቀረበውን መሆኑን ጠቅሰዋል።


የዘር ጥራትና ደህንነቱ በላብራቶሪ ተፈትሾና ተረጋግጦ በህብረት ስራ ማህበራትና በዘር አብዢዎች አማካኝነት ለአርሶ አደሩ የሚሰራጨው ምርጥ ዘርም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል።

አርሶ አደሩም ጥራትና ደህንነቱ የተረጋገጠ ዘር ገዝቶ በመጠቀም ምርታማነቱን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነቱን ለማረጋገጥ እንዲሰራ መክረዋል።


‎የክልሉ ግብርና ቢሮ የዘር ብዜት ባለሙያ አቶ ጥላዬ ሞገሴ እንዳሉት ከባለስልጣኑ ጋር በመተባበር ለአርሶ አደሩ የሚቀርበውን ዘር ጥራት በማረጋገጥ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት እየተሰራ ነው።

በዚህም አርሶ አደሩ በህገወጥ መንገድ ዘርን ገዝቶ እንዳይጠቀም ተከታታይ ትምህርት በባለሙያዎች እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ በዘንድሮው የመኸር አዝመራ ከ5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች በዘር እንደሚሸፈን ከክልሉ ግብርና ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026