የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ ጥራትና ደህንነቱ የተረጋገጠ ከ169 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር እየተሰራጨ ነው 

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህርዳር ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ለ2018/19 የምርት ዘመን ጥራትና ደህንነቱ የተረጋገጠ ከ169 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ እየተሰራጨ መሆኑን የክልሉ የግብርና ጥራትና ደህንነት ባለስልጣን አስታወቀ።

‎የባለስልጣኑ ምክትል ኃላፊ አቶ ዘላለም ልየው ለኢዜአ እንደገለፁት፤ጥራትና ደህንነቱ በላብራቶሪ የተረጋገጠ ዘር ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግ የክልሉን ምርታማነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።


በዚህም ለ2018/2019 የምርት ዘመን ጥቅም ላይ የሚውል ከ169 ሺህ ኩንታል በላይ የበቆሎ፣ ስንዴ፣ ማሽላ፣ ጤፍና ሌሎች የሰብል ዘር ጥራትና ደህንነት በላብራቶሪ በማረጋገጥ እየተሰራጨ መሆኑን ገልጸዋል።

የዘር ጥራትና ቁጥጥር ስራው የተካሄደው በአማራ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ፣ በግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን፣ በዩኒየኖችና በግል ዘር አብዢዎች የቀረበውን መሆኑን ጠቅሰዋል።


የዘር ጥራትና ደህንነቱ በላብራቶሪ ተፈትሾና ተረጋግጦ በህብረት ስራ ማህበራትና በዘር አብዢዎች አማካኝነት ለአርሶ አደሩ የሚሰራጨው ምርጥ ዘርም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል።

አርሶ አደሩም ጥራትና ደህንነቱ የተረጋገጠ ዘር ገዝቶ በመጠቀም ምርታማነቱን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነቱን ለማረጋገጥ እንዲሰራ መክረዋል።


‎የክልሉ ግብርና ቢሮ የዘር ብዜት ባለሙያ አቶ ጥላዬ ሞገሴ እንዳሉት ከባለስልጣኑ ጋር በመተባበር ለአርሶ አደሩ የሚቀርበውን ዘር ጥራት በማረጋገጥ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት እየተሰራ ነው።

በዚህም አርሶ አደሩ በህገወጥ መንገድ ዘርን ገዝቶ እንዳይጠቀም ተከታታይ ትምህርት በባለሙያዎች እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ በዘንድሮው የመኸር አዝመራ ከ5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች በዘር እንደሚሸፈን ከክልሉ ግብርና ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026