🔇Unmute
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 27/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን አሲዳማ አፈርን በኖራ በማከም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው ሃላፊ አቶ ጥላሁን ንጋቱ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በመጪው መኸር ምርትና ምርታማነትን በሁሉም አማራጭ በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል ርብርብ እየተደረገ ነው።

በዚህም ከ46 ሺህ ሄክታር በላይ በአሲድ የተጠቃ መሬትን በኖራ በማከም ቀድሞ ወደ ነበረበት ምርታማነት ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በኖራ አቅርቦት ዙሪያ ከአቅራቢ ድርጅቶች ጋር በመነጋገር በፍጥነት ለአርሶ አደሩ ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን የገለጹ ሲሆን እስካሁን ከ3ሺህ ኩንታል በላይ ኖራ ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን ተናግረዋል።
በቀጣይ ወራትም አስፈላጊውን መጠን ኖራ በማቅረብ አሲዳማ የሆነውን አፈር የማከሙ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
በመኸር ምርቱ የታቀደውን የምርት ጭማሪ ለማስመዝገብም መሬትን በኖራ ከማከም ባሻገር አዳዲስ አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም ላይ በማተኮር እየተሰራ ነው ብለዋል።

በዞኑ የማቻከል ወረዳ የቅዳማን ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ባየልኝ ሙላት እንደገለጹት በአሲድ የተጠቃውን አንድ ሄክታር ማሳቸውን በኖራ በማከም ዘር እየዘሩ ነው።
በኖራ አክመው ከሚዘሩት ሰብል ከአምስት ኩንታል በላይ የምርት ጭማሪ እንዳገኙ ጠቁመው ያገኙትን ጥቅም ለማሳደግም ዘንድሮ ከ30 ኩንታል በላይ ኖራ ማሳቸው ላይ መበተናቸውን ተናግረዋል።
በአነደድ ወረዳ የጉዳለማ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ጊዜአለው አግደውም ማሳቸውን በኖራ በማከም ለምነቱ እንዲመለስ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
አሁን ላይም ከግማሽ ሄክታር በላይ ማሳቸው ላይ ኖራ በመበተን ደጋግመው ማረሳቸውን ጠቁመው በቀጣይም ከዘሩ ጋር ቀላቅለው በመዝራት ምርታማነታቸውን ለማሳደግ እንደሚሰሩም አመልክተዋል።
በመጪው የመኸር ምርት ከ660 ሺህ ሄክታር በላይ መሬትን በተለያዩ ሰብሎች በማልማት ከ26 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱ ተመልክቷል።
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026
አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...
Jul 24, 2026
ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...
Jul 16, 2026