የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማት የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል

May 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ሚያዚያ28/2018(ኢዜአ)፦ የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሃዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ።

የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ዛሬ ለህዝብ ይፋ ተደርጓል።

ከንቲባው በዚህ ወቅት እንደገለጹት የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት ሀይቁን ለትውልድ በሚተርፍ መልኩ አልምቶ ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችል መሆኑንናይፋ የተደረገው ዲዛይን በሀይቁ ላይ የሚሰሩ የልማት ሥራዎችን አካቶ የያዘ መሆኑን ተናግረዋል።


ከጥቁር ውሃ እስከ ታቦር ተራራ ድረስ የሚለማውና 12 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት ከተማዋን በሀገር አቀፍ ደረጃ ካሉ ከተሞች ጋር ተወዳዳሪና ተመራጭ እንድትሆን ያደርጋታል ብለዋል።

ከተማዋ በርካታ የተፈጥሮ ሀብቶች ባለቤት ናት ያሉት ከንቲባው ሀይቁን በአካባቢው ካለው ታቦር ተራራ፣ ፍል ውሀዎች፣ ፏፏቴዎችና ከወንዶ ገነት ጋር በማስተሳሰር አልምቶ የቱሪስት ማዕከል ለማድረግ ይሰራል ነው ያሉት።

በሀይቅ ዳርቻ ልማቱ የጥቁር ውሀ አካባቢ፣ በተለምዶ ፍቅር ሀይቅ ተብሎ የሚጠራው የመዝናኛ ስፍራ፣ የሀዋሳ አሳ ገበያ እና አሞራ ገደል አካባቢ ተካትተው አብረው ይለማሉ ብለዋል።

የሀይቅ ዳር ልማት ሥራው የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማማከር አገልግሎት በመስጠት እየሰራ መሆኑም ተጠቁሟል።

ዲዛይኑን ይፋ ለማድረግ በተዘጋጀ መርሀ ግብር የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፣ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አብርሃም ማርሻሎ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ በየነ በራሳን ጨምሮ ሌሎች የክልሉና የከተማዋ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች እና ባለሀብቶች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026