የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ከጉጂ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ18 ሺህ ቶን በላይ የቡና ምርት ለማእከላዊ ገበያ ቀርቧል

May 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዶላ፤ ግንቦት 4/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በዘንድሮው ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ18 ሺህ ቶን በላይ ጥራቱን የጠበቀ የቡና ምርት ለማእከላዊ ገበያ መቅረቡን የዞኑ ንግድ ጽህፈት ቤት ገለጸ።

ልዩ ጣዕም ያለውን ቡና በማምረት ለዓለም ገበያ በማቅረብ ላይ ከሚገኙ የኢትዮጵያ አካባቢዎች አንዱ የጉጂ ዞን ነው።

በዞኑ አብዛኛው የቡና ልማት በተፈጥሮ ደኖች ጥላ ስር የሚከናወን በመሆኑ፣ ምርቱ ተፈጥሯዊ (Organic) ይዘቱን ሳይለቅ እንዲያድግ ይረዳዋል።

በዞኑ ንግድ ጽህፈት ቤት የእቅድና በጀት ባለሙያ ደረሰ ደንቆ ለኢዜአ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ ከዞኑ ከ75 ሺህ ቶን በላይ የቡና ምርት ለማእከላዊ ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል።

በዞኑ የሚገኙ 36 የቡና ምርት አቅራቢዎች ምርቱን በብዛትና በጥራት እያዘጋጁ ለማእከላዊ ገበያ በማቅረብ ላይ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 18 ሺህ 682 ቶን ጥራቱንና ደረጃውን የጠበቀ ታጥቦ የተቀሸረ ደረቅ የቡና ምርት ለማእከላዊ ገበያ መቅረቡን ገልጸዋል።

ዘንድሮ ለገበያ ለማቅረብ የታቀደው ምርት ከዓምና ጋር ሲነጻጸር እድገት ማሳየቱንም ተናግረዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በዞኑ የቡና ጣእም ቅምሻ ማእከል መቋቋሙን ገልጸው፤ ማዕከሉ የቡና ምርት ጥራትና ብዛትን በመጨመር በአምራቾች ዘንድ መነሳሳት መፍጠር መቻሉን አንስተዋል።

በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የቡናና ሻይ ልማት ባለሙያ አቶ ብርሃኑ ፈይሳ በበኩላቸው የቡና ልማቱን ለማስፋት የተሻለ ምርት የሚሰጡ የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች ለአርሶ አደሩ እየቀረበ ይገኛል።

በዚህ ዓመት ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ጠቅሰው፣ በልማቱም ከ108 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች በመሳተፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

የአዶላ ከተማ ነዋሪና የቡና አምራች አቶ ጌታቸው ጎልጃ በሰጡት አስተያየት፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በተሻሻለው የቡና ልማትና ግብይት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

የቡና ጣእምና የቅምሻ ማእከል በአካባቢያቸው መቋቋሙን ተከትሎ የቡና ምርቱን በብዛት እና በጥራት በማምረትና ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆኑንም አመልክተዋል።

ሌላው የቡና አቅራቢ የሆኑት አቶ ኤልያስ ሰንጋጎ ከዘርፉ ገቢያቸውን ለማሳደግ ለምርት ጥራት ትኩረት መስጠታቸውን አስታውቀዋል።

የጉጂ ዞን ከ377 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና ተከል መሸፈኑ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026