🔇Unmute
አዳማ፤ ግንቦት 4/2018(ኢዜአ)፦ በክልሉ በመጪው ክረምት በሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአቮካዶ ተክል እንደሚሸፈን የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ገለፀ።
በቢሮው የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ኃላፊ ሙሐመድሳኒ አሚን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ የተሻሻሉ የአቮካዶ ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግ የአቮካዶ ልማት ኢኒሼቲቭን ውጤታማ ለማድረግ እየተሰራ ነው።
በመጪው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም አስር አይነት የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች ተዘጋጅቷል ነው ያሉት።
በተለይም አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ዘይቱን፣ ፓፓያ፣ ግሽጣ፣ ብርቱካን፣ አፕል፣ ሎሚና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልፀዋል።
በክልሉ የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በማዳቀል የችግኝ ዝግጅት ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት።
በክልሉ እስካሁን ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመደበኛና በተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች መሸፈኑንም ገልጸዋል።
በተለይ ለወጪ ንግድ የሚሆን አቮካዶ ልማትን ለማሳደግና ምርትና ምርታማነቱን ማሳደግ ለሚያስችሉ ስራዎች ትኩረት መሰጠቱን ጠቁመው በሁሉም የክልሉ ዞኖች፣ ከተሞችና ወረዳዎች በክላስተርና በመደበኛነት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026
አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...
Jul 24, 2026
ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...
Jul 16, 2026