የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የታሪክ፣ የፅናት፣ የሀገር ግንባታ ውጤትና የአፍሪካውያን የትስስር ተምሳሌት ነው

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ አየር መንገድ የታሪክ፣ የፅናት፣ የሀገር ግንባታ ውጤትና የአፍሪካውያን የትስስር ተምሳሌት መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ የመሬት ላይ አውሮፕላን ትዕይንት (Static Air Show) መርሃ ግብር በአየር መንገዱ ቅጥር ግቢ አካሂዷል፡፡

እንዲሁም አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ የባህል ልውውጥ ወሳኝ ሚና እየተወጣ መሆኑን የሚያንፀባርቅ ዓለም አቀፍ የባህል ቀን በስካይ ላይት ሆቴል አክብሯል።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከተመሰረተ ጥቂት ወራት በኋላ የተቋቋመ ታሪካዊ ተቋም ነው፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም አቀፍና በአህጉር አቀፍ ደረጃ ህዝቦችን እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን የማሳለጥ ተልዕኮ ሰንቆ መነሳቱን አስታውሰዋል፡፡

አየር መንገዱ ባለፉት አስርት ዓመታት አፍሪካን ከቀረው ዓለም ጋር ድልድይ ሆኖ በማገናኘት መንገደኞችና ሸቀጦችን አጓጉዟል፤ ንግድና ኢንቨስትመንት፣ ቱሪዝምና ዲፕሎማሲ እንዲሳለጥ አድርጓል ብለዋል፡፡

የአፍሪካ ቀዳሚ የአቪዬሽን ግሩፕ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ፈጣን እድገት እያስመዘገቡ ካሉ አየር መንገዶች አንዱ መሆን መቻሉንም ገልጸዋል፡፡

መንግስት ሁሉን አቀፍ ሪፎርም በማድረግ የዘርፉን መሰረተ ልማት በማዘመን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍ የሀገራዊ ለውጥ አጀንዳ ማዕከል እንዲሆን አድርጓል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢኮኖሚ ስትራቴጂያዊ ምሰሶና የአፍሪካውያን የኩራት ምንጭ መሆኑን ጠቅሰው፤ በኢትዮጵያ በአቪዬሽንና ሎጂስቲክስ ያላትን መሪነት የሚያጠናክሩ ፖሊሲዎች ገቢራዊ እንደሚደረጉ ገልጸዋል፡፡

የአውሮፕላን ትዕይንቱ አየር መንገዱ ባለፉት ዓመታት ያስመዘገበውን የቴክኖሎጂ እድገትና የብቃት ጉዞ የሚያሳይ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የአቪዬሽን፣ ዘመናዊ የሎጂስቲክስ ስርዓት እና በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስር ወደላቀ አህጉራዊ ውህደት ለመሸጋገር በትጋት እንሰራለን ብለዋል፡፡

ለአየር መንገዱ ስኬታማ ጉዞ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቀድሞና የአሁኑ መሪዎች፣ ፓይለቶች፣ መሐንዲሶችና ለመላው ሰራተኞች ምስጋና አቅርበዋል።

አየር መንገዱ በአምስት አህጉራት፣ በ82 ሀገራት እና በ140 መዳረሻዎች በረራ በማድረግ ሰዎችን በማገናኘትና ባህላዊ ትስስር በመፍጠር ረገድ አስደናቂ ሚና እየተወጣ መሆኑ ይታወቃል።

አየር መንገዱ ላለፉት 80 ዓመታት ዘመናዊ አውሮፕላኖችን በመጠቀም በአፍሪካ ሰማይ ላይ ቀዳሚ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026