የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮ የምርት ዘመን ከ89 ሺህ ኩንታል በላይ የሻይ ምርት ለገበያ ቀርቧል

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮው የምርት ዘመን በ1 ሺህ 280 ሄክታር መሬት ላይ ከለማው ሻይ ከ89 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለገበያ መቅረቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በቢሮው የፍራፍሬ ልማት ዳይሬክተር አቶ ቻላቸው አዱኛ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ የሻይ ልማት ኢንሼቲቭ ተቀርጾ ወደ ሥራ ከተገባ ወዲህ የአርሶ አደሩ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መጥቷል።

የክልሉ መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት፣ የምርት ጥራትና ብዛትን የሚጨምሩ የተሻሻሉ የሻይ ዝርያዎች ለአርሶ አደሩ እንዲቀርቡ ተደርጓል ብለዋል።

የሻይ ልማቱ በስፋት እየተከናወነ የሚገኘው የክልሉን ዞኖች መልክዓምድርና ተስማሚ የአየር ንብረት መሰረት አድርጎ መሆኑን ገልጸው፤ በተለይም በጅማ፣ ኢሉባቦር እና ቡኖ በደሌ ዞኖች ውስጥ መሆኑን ጠቁመዋል።

ልማቱን ይበልጥ ለማሳደግ የተሻሻሉ ዝርያዎች የሚባዙባቸው የሻይ ችግኝ ጣቢያዎች በመንግስትና በአርሶ አደሮች ደረጃ ተዘጋጅተው ወደ ሥራ ገብተዋል ብለዋል።

ባለፉት 9 ወራት ለገበያ የቀረበው ከ89 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ክልሉ በዘርፉ ያለውን እምቅ አቅም የሚያሳይ መሆኑን አቶ ቻላቸው ገልጸዋል።

ባለፉት ሦስት ዓመታት አርሶ አደሮች በዘርፉ ወደ ኢንቨስትመንት እንዲሸጋገሩ በተደረገው ጥረት እስካሁን 10 አርሶ አደሮች ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገር መቻላቸውንም አስረድተዋል።

በቀጣይም ዘርፉን ይበልጥ ለማዘመን እና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሻይ ምርት ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን ግንባታ ማፋጠን እና ለምርቱ አስተማማኝ የገበያ ትስስር መፍጠር ትኩረት የተሰጣቸው ተግባራት መሆናቸውንም ገልጸዋል።

ይህ የሻይ ልማት እንቅስቃሴ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ፣ በባለሀብቶችና በአርሶ አደሮች መካከል ያለውን ቅንጅት በማጠናከር ረገድ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ዳይሬክተሩ አክለው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026