የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮ የምርት ዘመን ከ89 ሺህ ኩንታል በላይ የሻይ ምርት ለገበያ ቀርቧል

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮው የምርት ዘመን በ1 ሺህ 280 ሄክታር መሬት ላይ ከለማው ሻይ ከ89 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለገበያ መቅረቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በቢሮው የፍራፍሬ ልማት ዳይሬክተር አቶ ቻላቸው አዱኛ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ የሻይ ልማት ኢንሼቲቭ ተቀርጾ ወደ ሥራ ከተገባ ወዲህ የአርሶ አደሩ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መጥቷል።

የክልሉ መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት፣ የምርት ጥራትና ብዛትን የሚጨምሩ የተሻሻሉ የሻይ ዝርያዎች ለአርሶ አደሩ እንዲቀርቡ ተደርጓል ብለዋል።

የሻይ ልማቱ በስፋት እየተከናወነ የሚገኘው የክልሉን ዞኖች መልክዓምድርና ተስማሚ የአየር ንብረት መሰረት አድርጎ መሆኑን ገልጸው፤ በተለይም በጅማ፣ ኢሉባቦር እና ቡኖ በደሌ ዞኖች ውስጥ መሆኑን ጠቁመዋል።

ልማቱን ይበልጥ ለማሳደግ የተሻሻሉ ዝርያዎች የሚባዙባቸው የሻይ ችግኝ ጣቢያዎች በመንግስትና በአርሶ አደሮች ደረጃ ተዘጋጅተው ወደ ሥራ ገብተዋል ብለዋል።

ባለፉት 9 ወራት ለገበያ የቀረበው ከ89 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ክልሉ በዘርፉ ያለውን እምቅ አቅም የሚያሳይ መሆኑን አቶ ቻላቸው ገልጸዋል።

ባለፉት ሦስት ዓመታት አርሶ አደሮች በዘርፉ ወደ ኢንቨስትመንት እንዲሸጋገሩ በተደረገው ጥረት እስካሁን 10 አርሶ አደሮች ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገር መቻላቸውንም አስረድተዋል።

በቀጣይም ዘርፉን ይበልጥ ለማዘመን እና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሻይ ምርት ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን ግንባታ ማፋጠን እና ለምርቱ አስተማማኝ የገበያ ትስስር መፍጠር ትኩረት የተሰጣቸው ተግባራት መሆናቸውንም ገልጸዋል።

ይህ የሻይ ልማት እንቅስቃሴ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ፣ በባለሀብቶችና በአርሶ አደሮች መካከል ያለውን ቅንጅት በማጠናከር ረገድ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ዳይሬክተሩ አክለው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026