የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ዩኒቨርሲቲው የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030"ን ሀገራዊ ራዕይ ለማሳካት በትኩረት እየሰራ ነው 

May 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ዩኒቨርሲቲውየመንግሥት ተቋማትን የዲጂታላይዜሽን አቅም በማሳደግ የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030"ን ሀገራዊ ራዕይ ለማሳካት በትኩረት እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ንጉሥ ታደሰ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን በተያዘው በጀት ዓመት ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል።

የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገትን ከመተንበይ ባለፈ የፋይናንስ አካታችነትን ያረጋግጣል፣ ለወጣቶች ሰፊ የስራ እድል ይፈጥራል፣ እንዲሁም የመንግስት አሰራርን በማሳለጥ የዜጎችን ህይወት ያቃልላል።

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ከግብ ለማድረስም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና ከፍተኛ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ንጉሥ ታደሰ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን ተወዳዳሪነት ይበልጥ ለማሳደግ በዲጂታላይዜሽን ራሷን ለማብቃት እየተጋች ነው፡፡

ይህ እውን እንዲሆን ደግሞ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና እጅግ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።

የመንግሥት ተቋማትን አሰራር ማዘመን እና የአገልግሎት አሰጣጥን ማቀላጠፍ ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከተሰጡት ሀገራዊ ተልዕኮዎች መካከል ቀዳሚው በመሆኑ ይህንን ለማሳካት የዲጂታላይዜሽን አማራጭ ፍቱን መፍትሄ ነው ብለዋል፡፡

የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ልማት ለማፋጠን እየተተገበረ ያለውን የዲጂታል ስትራቴጂ ስኬታማ ለማድረግ፣ ተቋሙ የመንግሥት ተቋማትና ቴክኖሎጂ የሚተሳሰሩበትን አቅም ለመገንባት በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።

ከእነዚህም መካከል የዩኒቨርሲቲውን የውስጥ አሰራርና የስልጠና አሰጣጥ ሥርዓት ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ማድረግና የመንግሥት ተቋማት የዲጂታል አሰራርን የተላበሰ አገልግሎት መስጠት የሚችሉበትን አቅም ለመፍጠር የሚያስችል ልዩ ኮሌጅ በማደራጀት ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

እንዲሁም በዘርፉ ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ መምህራንን የማፍራት ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የመንግሥት ተቋማት ሥራቸውን ውጤታማ በሆነ መንገድ ማከናወን እንዲችሉ ከዲጂታል ዘርፍ ጋር የተቆራኙ አዳዲስ የስልጠና ፕሮግራሞችን ለመክፈት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ለአብነትም የአይቲ ኢንፍራስትራክቸር እና ሳይበር ሴኪውሪቲ ትምህርት ክፍልን ለመክፈት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በመንግሥት ተቋማት ውስጥ የዲጂታል አገልግሎትን ማስፈንና በዘርፉ ብቁ የሰው ኃይል ማፍራት ከተቻለ፣ የመንግሥትን አሰራር ከማዘመንም ባለፈ ብልሹ አሰራርንና ሙስናን በዘላቂነት ለመቅረፍ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026