የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ሀዋሳ ከተማን ለነዋሪዎች ምቹ እና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የሚያደርጉ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናክሮ ይቀጥላል

May 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን ለነዋሪዎች ምቹ እና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የሚያደርጉ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ ከከተማው ከንቲባና ከተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች ጋር በመሆን፤ በከተማዋ ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።


ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በምረቃው መርሃ ገብር እንዳሉት፤ የለውጡ መንግስት ለከተሞች በሰጠው ልዩ ትኩረት የከተሞችን ዕድገት የሚያፋጥኑ ዘርፈ-ብዙ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።

በዚህም ሀዋሳን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ደግሞ ተመራጭ ለማድረግ የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።


በከተማዋ የተመረቁት የልማት ፕሮጀክቶች በኮሪደር ልማት የተጀመሩ ሥራዎችን ከማጠናከር ባለፈ፤ የአገልግሎት አሰጣጥን በማሳለጥ የሕዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች የሚመልሱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የክልሉ መንግስት ሀዋሳን የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ለቱሪዝም መስህብ ልማቶችና ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ማስፋፊያ ልዩ ትኩረት መስጠቱንም አንስተዋል።


የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው፤ የሀዋሳን የኮሪደር ልማትና ሁሉን አቀፍ የልማት ፕሮጀክቶች በማፋጠን ከተማዋን የቱሪዝምና የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በከተማዋ በመደመር እሳቤ የሚከናወኑት የልማት ፕሮጀክቶች በተለይም በጥራት ላይ ማተኮራቸውን አብራርተዋል።

ዛሬ ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ማስፋፊያ፣ የአጠቃላይ ትምህርት ቤቶች ማስፋፊያ ግንባታ እና ሌሎች መሰረተ-ልማቶች ይገኙበታል ብለዋል።

እነዚህ ፕሮጀክቶች በአጠቃላይ ከ2 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው መሆኑን ከንቲባው አስታውቀዋል።


የሃዋሳ ከተማ ነዋሪዋ ሲስተር እልፍነሽ ናኡሼ፤ በሃዋሳ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች ከተማዋን አዲስ ገጽታ እያላበሷት መሆኑንና የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለነዋሪዎች አዲስ የሥራ ዕድል እየፈጠሩ እንደሚገኙ አክለዋል።


ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ተስፋዬ አበባው፤ ዛሬ በከተማዋ የተመረቁት ፕሮጀክቶች በተለይም በጤናው ዘርፍ የነበሩትን ውስንነቶች ከመቅረፍ አንጻር ትልቅ ሚና እንደሚኖራቸው ገልጸዋል።

በምረቃ መርሃ-ግብሩ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)፣ የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና የሕብረተሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026