የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ዜጎች የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ የተጀመረው ጥረት ይቀጥላል

Jun 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወራቤ ፤ ግንቦት 26/2018(ኢዜአ)፦የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥን በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ተደራሽ በማድረግ ዜጎች የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በስልጤ ዞን በወራቤ ከተማ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን መርቀው ዛሬ ሥራ አስጀምረዋል።


በማዕከሉ በአሁኑ ወቅት ከ6 የተለያዩ ተቋማት 20 አገልግሎቶች የሚሰጡ መሆናችውን ገልጸው በቀጣይ ይበልጥ እየሰፋ የሚሄድ ስለመሆኑ አንስተዋል።

በመሆኑም በሁሉም አካባቢዎች ተደራሽ በማድረግ ዜጎች የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ በበኩላቸው እንዳሉት፡ መንግስት በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ውስንነቶችን ለመፍታት ዲጂታል የመንግስት አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ ላይ ነው።

በዞኑ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዞ መስጠት ስለመጀመሩም ጠቁመዋል።


ዛሬ በወራቤ ከተማ ተገንብቶ የተጠናቀቀው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቋት በመስጠት የማህበረሰቡን እንግልት ያስቀራል ብለዋል።

የወራቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ያሲን ከሊል እንደገለፁት፤ መንግስት ሰው ተኮር ፕሮጀክቶችን እውን በማድረግ የማህበረሰቡን ችግር ለመፍታት በቅንጅት እየሰራ ይገኛል።

በወራቤ ከተማ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግርን ለመቅረፍ በ260 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተገነባው መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የዚሁ አካል መሆኑንም ተናግረዋል።

በተመሳሳይ ርዕሰ መስተዳድሩ በከተማዋ ሳምንቱን ሙሉ አገልግሎት መስጠት የሚችል የገበያ ማዕከልም መርቀው ስራ አስጀምረዋል።


የምርት አቅርቦት ችግር ለመፍታት ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃው ዘመናዊ የግብይት ማዕከሉ የከተማዋን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ተጨባጭ ውጤት እንደሚያመጣ ተመላክቷል።

በመርሐ ግብሩ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ፣ የክልሉና የስልጤ ዞን ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የከተማው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026