🔇Unmute
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል ለህዝቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለፁ፡፡
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ሀዋሳን ጨምሮ በተለያዩ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን ጎብኝተዋል፡፡

ርእሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ ለህዝቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡
በክልሉ የሲዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በይፋ ሥራ ከጀመረ በኋላ ባሉት ዘጠኝ ወራት ከ50 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት መሰጠቱን ጠቁመዋል፡፡
በዚህም ተገልጋዮች በማእከሉ በተሰጣቸው አገልግሎት እርካታ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።
አገልግሎቱን ወደ ሁሉም አካባቢዎች ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በቅርቡ ስራ የጀመረውን የሀዋሳ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ለአብነት ጠቅሰዋል።

በሌሎች የክልሉ ከተሞችም አገልግሎቱን በማስፋት ህዝቡ ሳይንገላታ የተቀላጠፈ አገልግሎት በቀላሉ እንዲያገኝ ለማስቻል እየተሰራ መሆኑን ገልፀው በግንባታ ላይ ያሉና በአጭር ጊዜ ውስጥ ለአገልግሎት የሚበቁ ማዕከላት መኖራቸውን አመልክተዋል፡፡
በሲዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመገኘት ከተገለገሉ ነዋሪዎች መካከል አቶ ወንደሰን አሸቴ፤በማዕከሉ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ወደ ማዕከሉ በመጡ በ30 ደቂቃ ውስጥ የሚፈልጉትን አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ማግኘታቸውን ገልፀዋል፡፡
በማዕከሉ የአሻራ አገልግሎት እንዳገኙ የተናገሩት አቶ ፈጠነ አድማሱ በበኩላቸው በአጭር ጊዜ የተቀላጠፈ አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡
ጉዳያቸውን በጊዜ ጨርሰው ወደ ሌላ የዕለት ተግባራቸው መሄድ እንደቻሉም አስረድተዋል፡፡

በአጭር ጊዜ ውስጥ ግልፅና የተቀላጠፈ አገልግሎት ማግኘት መቻሉ በራሱ ብልሹ አሰራሮችን ለማስቀረት ወሳኝ ሚና እንዳለው ተናግረዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ በጉብኝታቸው የሲዳማና የሀዋሳ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ማዕከላትን እንዲሁም በወንዶ ገነትና ለኩ ከተሞች እየተገነቡ ያሉ ማዕከላትን የተመለከቱ ሲሆን ሌሎች የክልል እና የከተማ አስተዳደሮች የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026
አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...
Jul 24, 2026
ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...
Jul 16, 2026