የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ከተለያዩ ሀገራት ጋር የተደረጉት ስምምነቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትና የአየር መንገዱን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ናቸው

Jun 5, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 27/2018(ኢዜአ)፦ ከተለያዩ ሀገራት ጋር የተደረጉት ስምምነቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትና የኢትዮጵያ አየር መንገድን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ መሆናቸውን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሠላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 23ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል።

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር)፤ ከተለያዩ ሀገራት ጋር የተደረጉት ስምምነቶች የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እና የአየር መንገዱን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ናቸው ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ ከሴራሊዮን ሪፐብሊክ፣ ከአንጎላ ሪፐብሊክ፣ ከባንግላዲሽ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ እና ከኢስዋቲኒ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ጋር ያደረገቻቸውን የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ ሪፖርቶችና የውሳኔ ሃሳቦችን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

እነዚህ የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆች ለንግድና ኢንቨስትመንት፣ ለቱሪዝም፣ ለዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች እንዲሁም የአየር ትራንስፖርት መዳረሻዎችን ለማስፋፋት ያላቸውን ከፍተኛ ጠቀሜታ አብራርተዋል።

በተጨማሪም ስምምነቶቹ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቁና በዘርፉ ያላትን ሚና በማጉላት ተጠቃሚነቷን የሚያሳድጉ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።

ምክር ቤቱም በቀረቡት ረቂቅ አዋጆች ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ አዋጆቹን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።

ከምክር ቤቱ አባላት በኩልም የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆቹ የአየር መንገዱን ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ጉልህ ሚና እንደሚኖራቸው ተገልጿል።

በሌላ በኩል፣ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመው ስምምነት ረቂቅ አዋጅም በምክር ቤቱ ጸድቋል።

የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር)፤ ስምምነቱ የሀገሪቱን ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠን፣ ለዓሳ ሀብት ልማት፣ ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ለማሳደግና በዘርፉ የግል ባለሀብቶችን ለመሳብ ጉልህ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።

በተጨማሪም የከፍተኛ ትምህርትና የምርምር ተቋማትን አቅም ለማሳደግና የምርምር ሥራዎችን ወደ ገበያ አውጥቶ ለማቅረብ ያለውን ጠቀሜታም አንስተዋል።

በተጨማሪም ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ዜጎች ቪዛን ለማስቀረት በተፈረመው የስምምነት ረቂቅ አዋጅ ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ፣ አዋጁን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026