የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በአማራ ክልል የኮሪደር ልማት የከተሞችን ገጽታ በመቀየር ኢንቨስትመንትና ቱሪዝምን እያነቃቃ ነው

Jun 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልድያ፤ ሰኔ 6/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለው የኮሪደር ልማት የከተሞችን ገጽታ በመቀየር ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ዘርፍ መነቃቃት አዲስ ምዕራፍ መክፈቱን የክልሉ ከተማና መሰረት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

የአማራ ክልል ከተማና መሰረት ልማት ቢሮ ክልላዊ የኮሪደር ልማት ልምድ ልውውጥና የግምገማ መድረክ በወልድያ ከተማ ተካሂዷል።

የቢሮ ኃላፊ ሞላ መልካሙ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት የክልሉ ከተሞችን ለነዋሪዎች፣ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።

በተለይም የመኪና፣ የብስክሌትና የእግረኛ መንገድ እንዲሁም የመዝናኛ የአረንጓዴ ስፍራና ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን አካቶ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን ለማፋጠን መሰረት እየጣለ ነው ብለዋል።

የኮሪደር ልማት በተካሄደባቸው አካባቢዎች ጠንካራ የቢዝነስና የኢንቨስትመንት ማዕከላት መፈጠራቸውን ገልጸው፤ ይህም ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት መነቃቃት ታላቅ ተስፋ ይዞ መጥቷል ብለዋል።

ባዛሬው የልምድ ልውውጥና የግምገማ መድረክም የተሻለ የሰሩ ከተሞች ለሌሎች ልምዳቸውን በማካፈል በቀጣይ ከተሞች ተቀራራቢ እድገት እንዲያስመዘገቡ ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርጫት ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍስሃ ደሳለኝ በበኩላቸው ከተሞችን በኮሪደር ልማት ለማስዋብና ገጽታቸውን ለመቀየር የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል ብለዋል።

ልማቱ የከተሞችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቀስቃሴ ከማሳደግ ባለፈ የገጠሩን እድገት ለማፋጠን እንደሚያስችለም አመልክተዋል።

የባህር ዳር ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ አስሜ ብርሌ በበኩላቸው፣ በባህር ዳር የተገነባው የኮሪደር ልማት የጣና ሐይቅን ጸጋ የገለጠና የከተማዋን ውበት ይበልጥ ያደመቀ መሆኑን ተናግረዋል።

የኮሪደሩ ልማቱ የተሽከርካሪ፣ የሳይክልና የእግረኛ መንገድ፣ የመዝናኛ ስፍራ፣ የአረንጓዴ ሰፍራና ሌሎች ልማቶችን ማካተቱን ጠቁመው ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል።

በጎንደር ከተማ አስተዳደር የከተማና መሰረት ልማት መምሪያ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉጌታ ታደሰ በጎንደር የተከናወነው የኮሪደር ልማት ለቱሪዝም እንቅስቃሴና ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ብለዋል።

በተለይ የፋሲል ግንብን፣ የሰሜን ተራሮችንና ሌሎች የመስህብ ስፍራዎችን ሊጎበኙ የሚመጡ የውጭና የአገር ውስጥ ቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜ በማራዘም አዎንታዊ ለውጥ አምጥቷል ብለዋል።

ልማቱ የቀጣዩን ትውልድ እድገት ጭምር መሰረት ያደረገ መሆኑን ጠቁመው "መድረኩም ልምዳችንን ለሌሎች ከተሞች ለማጋራትና ክፍተታችን ለመሙላት ያስቻለ ነው" ብለዋል።

በኮሪደር ልማት ደሴ ከተማን ማስዋብና ማሳመር ተችሏል ያሉት ደግሞ የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ናቸው።

በመድረኩ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የክልል፣ የከተማና የዞን አመራሮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026