🔇Unmute
አሶሳ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ (ቤጉ) መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አዳዲስ አገልግሎቶችን በውስጡ በማካተት ለተገልጋዮች ያለውን ተደራሽነት እያሰፋ መሆኑ ተገለጸ።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እያደገ የመጣውን የንግድ፣ የግብርና እና የኢንቨስትመንት ፍላጎት ለማስተናገድ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቱን ለማዘመን በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
በዚህም ባለፈው ዓመት መጨረሻ ላይ በአምስት የክልል እና ሶስት የፌደራል ተቋማት 33 አገልግሎቶችን አካቶ ስራ የጀመረው "ቤጉ መሶብ" የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአሁኑ ሰዓት አገልግሎቱን በማስፋት ተደራሽነቱን እያሳደገ ይገኛል።
የቤጉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዳይሬክተር ኢንጂነር ሰመረ ጅራታ እንደተናገሩት፤ ማዕከሉ በአሁኑ ሰዓት 33 የነበሩትን አገልግሎቶች ወደ 42 በማሳደግ ዜጎች ሁሉንም አገልግሎቶች በአንድ ቦታ እንዲያገኙ ለማድረግ እየሰራ ነው።
ፍትህ ቢሮ እና የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት በማዕከሉ እየሰጧቸው ከሚገኙ አገልግሎቶች በተጨማሪ ውልን መርምሮ ማጽደቅ እና የመድን ፈንድ አገልግሎት መስጠትን የመሳሰሉ አዳዲስ የስራ ዘርፎችን በማካተት የተገልጋዮችን እርካታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።
በቅርቡም የክልሉ ማዕድን ቢሮን ጨምሮ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና ሌሎች ተቋማት ወደ ማዕከሉ እንዲገቡ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል።
ቤጉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እስካሁን ድረስ ከ28 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች አገልግሎት መስጠቱን ጠቁመው፤ የተገልጋዮች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱንም ተናግረዋል።
ቤጉ መሶብ በቅርቡ ስራ ለጀመረው አሶሳ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም አስፈላጊውን የሙያ ዕገዛ በማድረግ ማዕከሉ በፍጥነት ወደ ስራ እንዲገባ ማድረጉን አብራርተዋል።
በቅርቡም በባምባሲ፣ ግልገል በለስ እና ካማሽ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለማስጀመር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል።
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026
አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...
Jul 24, 2026
ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...
Jul 16, 2026