የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

"ቤጉ መሶብ" አዳዲስ አገልግሎቶችን በማካተት ተደራሽነቱን እያሰፋ ነው

Jun 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ (ቤጉ) መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አዳዲስ አገልግሎቶችን በውስጡ በማካተት ለተገልጋዮች ያለውን ተደራሽነት እያሰፋ መሆኑ ተገለጸ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እያደገ የመጣውን የንግድ፣ የግብርና እና የኢንቨስትመንት ፍላጎት ለማስተናገድ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቱን ለማዘመን በትኩረት እየሰራ ይገኛል።

በዚህም ባለፈው ዓመት መጨረሻ ላይ በአምስት የክልል እና ሶስት የፌደራል ተቋማት 33 አገልግሎቶችን አካቶ ስራ የጀመረው "ቤጉ መሶብ" የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአሁኑ ሰዓት አገልግሎቱን በማስፋት ተደራሽነቱን እያሳደገ ይገኛል።

የቤጉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዳይሬክተር ኢንጂነር ሰመረ ጅራታ እንደተናገሩት፤ ማዕከሉ በአሁኑ ሰዓት 33 የነበሩትን አገልግሎቶች ወደ 42 በማሳደግ ዜጎች ሁሉንም አገልግሎቶች በአንድ ቦታ እንዲያገኙ ለማድረግ እየሰራ ነው።

ፍትህ ቢሮ እና የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት በማዕከሉ እየሰጧቸው ከሚገኙ አገልግሎቶች በተጨማሪ ውልን መርምሮ ማጽደቅ እና የመድን ፈንድ አገልግሎት መስጠትን የመሳሰሉ አዳዲስ የስራ ዘርፎችን በማካተት የተገልጋዮችን እርካታ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።

በቅርቡም የክልሉ ማዕድን ቢሮን ጨምሮ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና ሌሎች ተቋማት ወደ ማዕከሉ እንዲገቡ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል።

ቤጉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እስካሁን ድረስ ከ28 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች አገልግሎት መስጠቱን ጠቁመው፤ የተገልጋዮች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱንም ተናግረዋል።

ቤጉ መሶብ በቅርቡ ስራ ለጀመረው አሶሳ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም አስፈላጊውን የሙያ ዕገዛ በማድረግ ማዕከሉ በፍጥነት ወደ ስራ እንዲገባ ማድረጉን አብራርተዋል።

በቅርቡም በባምባሲ፣ ግልገል በለስ እና ካማሽ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለማስጀመር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026