🔇Unmute
ሮቤ ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በባሌ ዞን በበልግ አዝመራ በኩታገጠም አሠራር ካለሙት የስንዴ ሰብል የተሻለ ምርት እየጠበቁ መሆኑን የሲናና ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ።
በዞኑ በበልግ ወቅት በተለያዩ ሰብሎች ከለማው ከ277 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ከ8 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል።
የሲናና ወረዳ አርሶ አደር የሆኑት አቶ አደም ሁሴን እንዳሉት፤ በዘንድሮው የምርት ወቅት ምርጥ ዘርና የተሻሻሉ የግብርና ፓኬጆችን በአግባቡ በመጠቀማቸው ከአንድ ሄክታር እስከ 65 ኩንታል ምርት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።
ባለፉት አራት ዓመታት በኩታገጠም አሠራር በመሳተፍ በሚያገኙት ገቢ የቤተሰባቸውን ኑሮ እንደቀየረውም አክለዋል።
ሌላው የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር አቶ አህመድ በከር በበኩላቸው፤ ቀደም ሲል በባህላዊ መንገድ ከአንድ ሄክታር ያመርቱ የነበረው የስንዴ ምርት ከ20 ኩንታል እንደማያልፍ አስታውሰዋል።
ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ የተሻሻሉ አሠራሮችን የመጠቀም ዝንባሌና ተግባሩም እየተሻሻለ በመምጣቱ ከአንድ ሄክታር ማሳ እስከ 60 ኩንታል የስንዴ ምርት ማምረት ላይ መድረሳቸውን አመልክተዋል።
በዘንድሮ የምርት ወቅት በተለይ በባለሙያዎች ምክር የታገዘ የፓኬጅ አጠቃቀም፣ በሽታን መቋቋም የሚችል ምርጥ ዘር በወቅቱ በመጠቀማችን የማሳችን ቁመና እጅግ ተስፋ ሰጪ ሁኔታ ላይ ይገኛል፤ የተሻለ ምርትም እንጠብቃለን ነው ያሉት።
የሲናና ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የመሬትና ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደበሌ ሐቤቤ እንደገለጹት፤ በወረዳው በበልግ ወቅት በኩታገጠም ከለማው 45 ሺህ ሄክታር የስንዴ ማሳ ከ3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል።

የአርሶ አደሩ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ልምድ ከጊዜ ወደ ጊዜ ማደግ ለምርታማነቱ መጨመር ዋነኛ ምክንያት መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የባሌ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሙአዊያ ፉአድ በበኩላቸው፤ በዞኑ የነበረው የዝናብ ስርጭት ለሰብል ልማቱ መሳካት ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን ጠቁመዋል።

በበልግ አዝመራ በተለያዩ ሰብሎች ከለማው ከ277 ሺህ ሄክታሩ የታቀደውን የ8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት የሚያግዙ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026
አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...
Jul 24, 2026
ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...
Jul 16, 2026