የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ረቂቅ አዋጁ ከፍተኛ ጥራት ያላቸው ወቅታዊ እና አስተማማኝ የስታቲስቲክስ መረጃዎች እንዲመነጩ ያስችላል

Jun 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጅ ከፍተኛ ጥራት ያላቸው ወቅታዊ እና አስተማማኝ መረጃዎች እንዲመነጩ፣ እንዲሰራጩና እንዲቀናጁ የሚያደርግ ብሔራዊ ስታቲስቲክስ ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችል መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ጥሩ ማር አባተ ገለጹ።

ቋሚ ኮሚቴው የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጅ 23/2018 ዙሪያ የአስረጂ መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩም ቋሚ ኮሚቴው ግልጽነትና ማብራሪያ በሚፈልጉ ጉዳዮች ዙሪያ ከሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርጓል።


የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አዋጅ ከፍተኛ ጥራት ያላቸው ወቅታዊ እና አስተማማኝ መረጃዎች እንዲመነጩ፣ እንዲሰራጩና እንዲቀናጁ የሚያደርግ ብሄራዊ ስታቲስቲክስ ሥርዓት መዘርጋት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።

ረቂቅ አዋጁ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በቦርድ እንዲመራ የሚደነግግ ሲሆን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር የፖሊሲ አቅጣጫ ቁጥጥር የሚያከናውንበት እንዲሁም ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ አሰራርን በመከተል መረጃ ማመንጨት፣ መተንተንና ጥቅም ላይ እንዲውል ማስቻል ከዓላማዎቹ መካከል ይገኙበታል።

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ጥሩማር አባተ እንዳሉት፤ ረቂቅ አዋጁ በጥናት ላይ ተመስርቶ ተቋማትን ባቀናጀ አግባብ መዘጋጀቱን አብራርተዋል።

የብሔራዊ የስታቲስቲክስ ሥርዓትን ለመዘርጋት እንደሚያስችል ጠቅሰው፥ ይህም የተቋማትን ሚናና ኃላፊነት በግልጽ የሚያስቀምጥ በመሆኑ የሥራ ድግግሞሽና መረጃ መፋለሶችን የሚያስቀር መሆኑን አስረድተዋል።

እንደ ጂኦስፓሻል፣ ዲጂታል፣ በሴንሰር ላይ የተመሰረቱ በመስኩ ያሉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል።

በማስረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ አሰጣጥን ለማጎልበት አዋጁ ዓይነተኛ ፋይዳ እንደሚኖረውም አመልክተዋል።


የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በከር ሻሌ(ዶ/ር) እንዳሉት፤ የመረጃ አመንጪዎችን ሚስጥራዊነት መጠበቅ በረቂቅ አዋጁ በግልጽ የተቀመጠ ድንጋጌ ነው።

ከመረጃ ጥራት ጋር በተያያዘም ተቋማት የሚያመነጩት መረጃ ትክክለኛና መሰረታዊ መርህን ተከትለው መረጃ እንዲያመነጩ የአቅም ግንባታ ተግባራት እንደሚከናወኑ አስረድተዋል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ በበኩላቸው፤ ረቂቅ አዋጁ ከዓለም አቀፍና አህጉራዊ የስታቲስቲክስ መርሆና ድንጋጌዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል።


ረቂቅ አዋጁ በስታቲስቲክስ መስክ የሚከናወኑ ተግባራትን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመጸፈም ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው ብለዋል።

ይሁን እንጂ የመረጃ ሰጪዎችን ማንነትና ሚስጥራዊነት መጠበቅ ለዘርፉ ሥራ መቃናት ቁልፍ ሚና አለው ያሉት ሰብሳቢው በአዋጁ የመረጃ አመንጪዎች ግለሰቦችና ተቋማት ሚስጥራዊነት መጠበቅ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026