የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኢትዮጵያ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ማንሠራራት ጠንካራ መሠረት እየገነባች ነው

Jun 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ማንሠራራት በመሠረተ ልማት፣ በተቋማዊ አቅምና በዲጂታል ክህሎት ጠንካራ መሠረት እየገነባች እንደምትገኝ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲጂታል አማካሪ ሚሪያም ሰዒድ ገለጹ።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት “ከለውጥ ወደ ዘላቂ ሽግግር” በሚል መሪ ሀሳብ የ“ኢትዮጵያ ታከናውናለች” ጉባኤ ተካሂዷል።


በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲጂታል አማካሪ ሚሪያም ሰዒድ፤ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ተበታትነው የቆዩ አሠራሮችን በዲጂታል ማንነት፣በክፍያ እና በዳታ ልውውጥ የተቀናጁ የኢኮኖሚ መዋቅሮች ውስጥ በማስገባት ለሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ምቹ የሆነ ምህዳር እየገነባች መሆኑን አመልክተዋል።


የመንግሥት አገልግሎቶችን በማገናኘት እንዲሁም የሀገር በቀል አቅምን በጋራ በማሳደግ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


ኢኮኖሚያዊ እድገት በምርት፣ በወጪ ንግድ እና በኢንቨስትመንት አቅሞች ላይ የተመሰረተ መሆኑን ገልጸው፤ ይህን ወደ ተሻለ ዕድገት ለማሸጋገር የዲጂታል አሠራሮች መጠናከር ተገቢ መሆኑን ተናግረዋል።


ኢትዮጵያ የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ የዲጂታል ስትራቴጂዎች ትግበራ በማዕድን፣ በግብርና፣ በከተሞች እና በመሠረተ ልማት ላይ ሰፊ በሆነ የኢኮኖሚ ሽግግር ውስጥ በስፋት እያሳየች መሆኑን ገልጸዋል።


የዲጂታል አገልግሎትን የሚያፋጥኑ መሠረተ ልማቶች ላይ ትኩረት አድርጎ መሠራቱ የክፍያ ሥርዓቶች በኢኮኖሚው ውስጥ የምዝገባ፣ የግብይት እና ሌሎች እንቅስቃሴዎች እንዲሳለጡ እያደረገ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።


ኢትዮጵያ ይህንኑ የዲጂታል ሪፎርም ወደ ምርታማነት ለመቀየር ለዘርፉ ዕድገት ማነቆ የሆኑትን የፋይናንስ ችግር፣የባለሙያዎች አቅም ውስንነት መፍታት ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል።


ሀገሪቱ ቴክኖሎጂ መጠቀም የሚችል ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራትም የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች መሆኗን ተናግረዋል።


በአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ በርካታ ዜጎችን የማብቃት ሥራ በስፋት እየተሠራ መሆኑንም አክለዋል።


ኢትዮጵያ ለሰው ሰራሽ አስተውሎት ልማትና ትግበራ የሚሆን ተቋማዊ፣ የሰው ሃይልና የቴክኖሎጂ አቅም ላይ ትኩረት መስጠቷንም አንስተዋል።


የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ፣በዓለም አቀፍ ደረጃ ልዩ ዩኒቨርሲቲ እንዲሆን፣ ሥርዓት ፈጣሪዎችን ለማሰልጠን እና ምርምርን ከተግባር ጋር ለማገናኘት የተነደፈ መሆኑንም አክለው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026