የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

መንግሥት በመደመር እሳቤ ዘመን ተሻጋሪና ሜጋ መሠረተ ልማቶችን እውን አድርጓል-ብሩክ ታዬ(ዶ/ር)

Jun 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦የለውጡ መንግሥት በመደመር እሳቤ ውጤታማ የፋይናንስ ሥርዓትን በመከተል ለትውልድ የሚሻገሩ ሜጋ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን እውን ማድረጉን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት "ከለውጥ ወደ ዘላቂ ሽግግር" በሚል መሪ ሀሳብ "ኢትዮጵያ ታከናውናለች" ጉባኤ በሳይንስ ሙዚየም ተካሂዷል።


የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ፥ የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት ጉዞ ለዘመናት ከዘለቀው ሀገራዊ ትልም ተነሥቶ፣ አሁን ላይ በትጉህና ግልጽ መርሆዎች እንዲሁም በተቀናጀ አፈጻጸም ወደሚመራ የለውጥ ዘመን መሸጋገሩን ገልጸዋል።

ለዚህ ስኬት ደግሞ የለውጡ መንግሥት ሀገራዊ ተስፋን ከተቋማዊ አቅም ጋር ወደሚያጣጥም፣ ይበልጥ አመቺ፣ ቅደም ተከተላዊ እና የፋይናንስ ሥርዓትን ወደ ተከተለ አካሄድ ቁርጠኛ ሽግግር በማድረጉ የተመዘገበ ነው ብለዋል።

የእያንዳንዱ ውጤት መሠረትም የለውጡ መንግስት የተከተለው የመደመር እሳቤ መሆኑን አስረድተዋል።

ይህ የመደመር እሳቤ አካሄድም መሠረተ ልማትን ወደ ቀጣይነት ያለው ሀገራዊ እሴት እና ለትውልድ ተሻጋሪ ሀብት እንዲቀየር እያደረገው እንደሚገኝ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አስታውቀዋል።

በተጨማሪም የታዳሽ ሃይል፣ የዲጂታል ማስፋፊያ፣ የትራንስፖርት፣ የኮንስትራክሽን እና የአረንጓዴ ቴክኖሎጂ ስትራቴጂካዊ ዘርፎች ሀገሪቱ የምታደርገውን የለውጥና የብልጽግና ጉዞ እየመሩት እንደሚገኙም ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ በራሷ አቅም ፈጣን እድገቷን ለማስቀጠል እየተጋች እንደምትገኝ በማብራሪያቸው ላይ አመላክተዋል።

በዚህም በርካታ ግዙፍ መሠረተ ልማቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት እየተደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል።

መንግስት መሠረተ-ልማትን በተመለከተ ውጤታማ የሆኑ አሠራሮችን በቀጣይነት በመተግበሩ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026