የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በኦሮሚያ ክልል በመኸር እርሻ እስካሁን ከ4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል  

Jun 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በመኸር እርሻው እስካሁን ከ4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ እንዳሻው ጀማነህ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ በመኸር እርሻ 11 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬትን በኩታገጠም በማልማት ከ380 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ ነው።


በክልሉ እስካሁን በተደረገው እንቅስቃሴ ከ9 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ታርሶ ለዘር መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

በዘንድሮው የመኸር እርሻ ወቅት በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች በዋናነት የጥራጥሬ እና የሰብል ዘር ዓይነቶች እየተዘሩ መሆኑን ገልጸዋል።

ታርሶ ለዘር ከተዘጋጀው መሬት ውስጥ እስካሁን 4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታሩ በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ተሸፍኗል ብለዋል።

ለመኸር እርሻ ከተዘጋጀው መሬት ውስጥ እስካሁን ከ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የሚሆነው በትራክተር ታግዞ መታረሱን ጠቁመዋል።

በክልሉ ለመኸር እርሻ ሥራው ከ14 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለማቅረብ ታቅዶ፣ እስካሁን ከ8 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ሕብረት ሥራ ማህበራትና በዩኒየኖች ጋር መድረሱን ገልጸዋል።


ለማህበራቱና ለዩኒየኖቹ ከደረሰው የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ ከ4 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ለአርሶ አደሩ መከፋፈሉን አንስተዋል።

እንዲሁም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ይረዳ ዘንድ የተለያዩ ምርጥ ዘሮች ለአርሶ አደሮቹ መቅረባቸውን አክለዋል።

በክልሉ በአሁኑ ወቅት ያለው የዝናብ ሁኔታ መልካም በመሆኑ አርሶ አደሩ ያለውን ምቹ ሁኔታ በአግባቡ በመጠቀም ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በክልሉ በመኸር እርሻው የታቀደውን ምርት ለማግኘት በየደረጃው ያሉ አመራሮችና ባለሙያዎች ለአርሶ አደሩ ድጋፍና ክትትል እያደረጉላቸው ይገኛሉ ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026