🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በመኸር እርሻው እስካሁን ከ4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ እንዳሻው ጀማነህ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ በመኸር እርሻ 11 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬትን በኩታገጠም በማልማት ከ380 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ ነው።

በክልሉ እስካሁን በተደረገው እንቅስቃሴ ከ9 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት ታርሶ ለዘር መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
በዘንድሮው የመኸር እርሻ ወቅት በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች በዋናነት የጥራጥሬ እና የሰብል ዘር ዓይነቶች እየተዘሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ታርሶ ለዘር ከተዘጋጀው መሬት ውስጥ እስካሁን 4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታሩ በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ተሸፍኗል ብለዋል።
ለመኸር እርሻ ከተዘጋጀው መሬት ውስጥ እስካሁን ከ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የሚሆነው በትራክተር ታግዞ መታረሱን ጠቁመዋል።
በክልሉ ለመኸር እርሻ ሥራው ከ14 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለማቅረብ ታቅዶ፣ እስካሁን ከ8 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ሕብረት ሥራ ማህበራትና በዩኒየኖች ጋር መድረሱን ገልጸዋል።

ለማህበራቱና ለዩኒየኖቹ ከደረሰው የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ ከ4 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ለአርሶ አደሩ መከፋፈሉን አንስተዋል።
እንዲሁም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ይረዳ ዘንድ የተለያዩ ምርጥ ዘሮች ለአርሶ አደሮቹ መቅረባቸውን አክለዋል።
በክልሉ በአሁኑ ወቅት ያለው የዝናብ ሁኔታ መልካም በመሆኑ አርሶ አደሩ ያለውን ምቹ ሁኔታ በአግባቡ በመጠቀም ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በክልሉ በመኸር እርሻው የታቀደውን ምርት ለማግኘት በየደረጃው ያሉ አመራሮችና ባለሙያዎች ለአርሶ አደሩ ድጋፍና ክትትል እያደረጉላቸው ይገኛሉ ብለዋል።
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026
አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...
Jul 24, 2026
ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...
Jul 16, 2026