የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ዲጂታላይዝድ መደረጉ አገልግሎቶችን በሚፈለገው ልክ ተደራሽ ማድረግ እያስቻለ ነው

Jun 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የወሳኝ ኩነት ምዝገባ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲታገዝ መደረጉ አገልግሎቶችን በሚፈለገው መልኩ ተደራሽ ማድረግ እያስቻለ መሆኑ የክልሉ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ አገልግሎት አስታወቀ።

የአገልግሎቱ ኃላፊ መዓዛ በዛብህ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በክልሉ የወሰኝ ኩነቶች መዝገባ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ በመደረጉ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ፍትሃዊና ተደራሽ ለማድረግ እያስቻለ ነው ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ 982 ሺህ 800 የልደት፣ የሞት፣ የጉዲፈቻ፣ የጋብቻና ፍች ኩነቶችን ለመስጠት ታቅዶ ከእቅድ በላይ 107 በመቶ ማከናወን መቻሉን ጠቅሰዋል።

የምዝገባ አገልግሎቱ ከሚሰጥባቸው ከ4 ሺህ የሚበልጡ ጣቢያዎች ውስጥ 570 የሚሆኑት በቴክኖሎጂ የተደራጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ለውጤቱም ጠንካራ የቅንጅት ስራ ከመኖሩ ባለፈ በተለያዩ አማራጮች ለማህበረሰቡ የተሰጠው የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች ተጠቃሽ መሆኑን ጠቁመዋል።

የህብረተሰቡን የአገልግሎት እርካታ የማሳደግና የቴክኖሎጂ አሰራርን ተደራሽ ለማድረግና በተሻለ መልኩ ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

የኩነቶች ምዝገባ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲደገፍ መደረጉ የመንግስትን ወጪ ከመቀነስ ባለፈ መረጃዎችን በጥራትና በፍጥነት ተደራሽ ማድረግ ማስቻሉን ጠቅሰዋል።

በክልሉ ባለፉት ዓመታት በተቀናጀ መንገድ በተሰራ ስራ ከ5 ሚሊየን በላይ ኩነቶችን መመዝገብ እንደተቻለም ኃላፊዋ አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026