የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በቱሪዝም ዘርፍ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን በማፍራት የሀገርን ኢኮኖሚና ገጽታ ለመገንባት የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

Jul 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በቱሪዝም ዘርፍ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን በማፍራት የሀገርን ኢኮኖሚና ገጽታ ለመገንባት የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ።

የፌደራል ቱሪዝም ኢንስቲትዩት “የላቀ ክህሎት ለቱሪዝም እድገት” በሚል መሪ ቃል 13ኛውን የቱሪዝምና የመስተንግዶ ሳምንት በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበር ጀምሯል።


በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ፣ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ፣ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዘርፉ ተዋናዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ መንግሥት በቱሪዝም ዘርፉ ውጤታማና ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት ሰፊ የሪፎርም ሥራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል።

ይህንን ማሻሻያ ተከትሎም የፌደራል ቱሪዝም ኢንስቲትዩትን የማጠናከር ሥራ የተሠራ ሲሆን፣ ተቋሙ ባለፉት ዓመታት በተለያዩ የቱሪዝም መስኮች ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ማፍራት መቻሉን ጠቁመዋል።

ኢንስቲትዩቱ ከመደበኛ ትምህርት በተጨማሪ አጫጭር ስልጠናዎችን በመስጠት ለበርካታ ዜጎች መድረስ መቻሉን ያነሱት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በዚህም ለብዙዎች የሥራ ዕድል እየተፈጠረ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በዘርፉ ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለውጭ ሀገራት ገበያም ተወዳዳሪ መሆን የሚችል የሰው ኃይል እየፈራ ይገኛል፤ ይህ ተግባር ይበልጥ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

ቱሪዝም ካለው ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ባሻገር ለሀገር ገጽታ ግንባታ ትልቅ ሚና እንዳለው ጠቅሰው በቀጣይም የአገልግሎት ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ በልዩ ትኩረት መሥራት ይገባል ብለዋል።

የቱሪዝምና መስተንግዶ ሳምንት መከበሩ፣ የሥራ ገበያውንና የሰለጠነውን የሰው ኃይል በቀጥታ ለማገናኘት እንዲሁም ዘርፉን ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዱ ጠቃሚ ግብዓቶችን ለመሰብሰብ ትልቅ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።


የፌደራል ቱሪዝም ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ በበኩላቸው፤ ተቋሙ በዘርፉ በርካታ ባለሙያዎችን በማፍራት ለኢንዱስትሪው ዕድገት የበኩሉን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝና በቀጣይም ይህንን ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የዘንድሮው የቱሪዝምና መስተንግዶ ሳምንትም ኢንስቲትዩቱን ይበልጥ ውጤታማ ሊያደርጉ በሚችሉና ዘርፉን በሚያሳድጉ የተለያዩ መርሃ ግብሮች እንደሚከበር ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026