የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የአገልግሎት እመርታ በመሶብ - የዜጎች እፎይታ እና የተሳለጠ አገልግሎት

Jul 2, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2018 (ኢዜአ)፡-የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የዜጎችን እንግልት በመቀነስ ፈጣን፣ ጥራት ያለውና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ማስቻሉን ተገልጋዮች ገለጹ፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተመርቆ ወደ ሥራ የገባው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የዜጎችን እንግልት በመቀነስና የመንግሥት አሰራርን በማዘመን ረገድ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ ነው።

ማዕከሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ አሰራርን በአንድ ቦታ ላይ በማቅረብ፣ ዜጎች የሚፈልጓቸውን አገልግሎቶች ያለምንም ውጣ ውረድ ፈጣን፣ ጥራት ያለውና ምቹ በሆነ ሁኔታ እንዲያገኙ አድርጓል።

ይህም የመንግሥትን አገልግሎት አሰጣጥ ከማሳለጡ ባለፈ፣ አጠቃላይ አሰራሩን ግልጽ በማድረግ ብልሹ አሰራርን በከፍተኛ ሁኔታ መከላከል ችሏል፡፡


የማዕከሉን አገልግሎት በተመለከተ ለኢዜአ አስተያየት የሰጡት የመዲናዋ ነዋሪ አቶ ደስታ ወዳጄነህ፣ የዲጂታል መሶብ አገልግሎት መዘርጋቱ ውድ ጊዜን የሚቆጥብና ኢትዮጵያ ወደ ላቀ የአገልግሎት ምዕራፍ እየገባች መሆኑን ማሳያ ነው ብለዋል።

አሰራሩ ዜጎች በቀላሉ አገልግሎት እንዲያገኙ በማስቻል ጊዜያቸውን በአግባቡ ለመጠቀም እንደረዳቸውና ቀደም ሲል ትልቅ ፈተና የነበረውን እንግልት ያስቀረ አሠራር መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡


ሌላኛው ነዋሪ አቶ ዮሴፍ ታመነ በበኩላቸው፣ ቀደም ሲል መታወቂያ ለማውጣት ብዙ መመላለስና አድካሚ ውጣ ውረዶች የነበሩ መሆኑን አስታውሰው፣ አሁን ግን በአዲሱ አሰራር ፈጣን አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

ረጅም ጊዜ ይወስድ የነበረው አገልግሎት በአሁኑ ወቅት በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ እንዲጠናቀቅ መደረጉ ነዋሪዎች በእለት ተእለት እንቅስቃሴያቸው ጊዜያቸውን እንዲቆጥቡና በቅልጥፍና እንዲስተናገዱ እንዳገዛቸው ጠቁመዋል፡፡

ይህም በአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ውስጥ ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችንና ተያያዥ ቅሬታዎችን ሙሉ በሙሉ ያስቀረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


ሌላኛዋ የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ ይርጋለም ተሾመ በበኩላቸው፣ የዲጂታል መሶብ አገልግሎት አሰጣጥ እጅግ የተራቀቀና ቅልጥፍና የተሞላበት በመሆኑ ለቀጣዩ ትውልድ ትልቅ መነሻ የሚሆን ነው ብለዋል።

ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር በአጠቃላይ በሀገሪቱ የአገልግሎት አሰጣጥ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠውና ለቀጣዩ ትውልድ መልካም አሻራ የሚጥል መሆኑንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።


ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ አስቻለው አድማሱ፣ የመሶብ አገልግሎት ቀደም ሲል በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የነበሩ በርካታና ውስብስብ ችግሮችን ያስወገደ መሆኑን ተናግረዋል።

ይህ ዘመናዊ የዲጂታል አሰራር በግለሰብ ደረጃ ምቾትን ከመፍጠሩ ባለፈ፣ እንደ ሀገርም ትልቅ እድገትና እምርታ መሆኑን በተጨባጭ ማረጋገጡን አስረድተዋል።

አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል መሰጠታቸው አላስፈላጊ መጉላላቶችን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚቀንስ የገለጹት ደግሞ ሌላኛው ነዋሪ አቶ ብርሃን አብርሃ ናቸው።


አቶ ብርሃን ከዚህ ቀደም የነበረው አሰራር እጅግ አድካሚና ውጣ ውረድ የበዛበት እንደነበር አስታውሰው፣ የአሁኑ ግን የተቀላጠፈና ምቹ መሆኑን መስክረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026