የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በሸገር ከተማ የኢንቨስትመንት መስፋፋት የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ የኢኮኖሚ ዕድገትን እያፋጠነ ነው

Jul 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሸገር ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦በሸገር ከተማ የኢንቨስትመንት መስፋፋት ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ የከተማዋን የኢኮኖሚ ዕድገት እያፋጠነው መሆኑን የከተማው አስተዳደር አስታወቀ።

አስተዳደሩ ይህንን የገለጸው ባለሀብቶችና ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈው 2ኛው ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ኤክስፖ ፎረም በተካሄደበት ወቅት ነው።


የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) በፎረሙ ላይ እንደተናገሩት፤ በዘርፉ የሚሰጡ የኢንቨስትመንት አገልግሎቶችና የአቀባበል ሥርዓቶችን ለማሻሻል ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ለውጥ ማምጣት ተችሏል።

ባለፉት ዓመታት ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት ምቹና ሳቢ ሁኔታዎችን በማመቻቸት የተሻለ ውጤት እየተገኘ መምጣቱንም ገልጸዋል።

የኢንቨስትመንት መስፋፋት የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ የኢኮኖሚ ዕድገትን እያፋጠነ መሆኑን ጠቅሰው፣ ከተማዋን የኢንቨስትመንት ማዕከል ለማድረግ የተጀመረው የተቀናጀ አሠራር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

የፎረሙ ዋና ዓላማ የኢንቨስትመንትን ውጤታማነት ማሳደግ መሆኑን የጠቀሱት ከንቲባው፤ በመንግሥትም ሆነ በባለሀብቶች በኩል የሚታዩ ጉድለቶችን በውይይት ለይቶ መፍትሔ ማስቀመጥ መቻሉን አስረድተዋል።

የሸገር ከተማ የኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ኃላፊ ኃይለሚካኤል ዓለሙ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ከተማዋ የኢንቨስትመንት ማዕከል እንድትሆን የሚያስችሏት በርካታ ምቹ ዕድሎች እንዳሏት ገልጸዋል።


ለአብነትም የከተማዋን የመሬት አስተዳደር በቴክኖሎጂ በማገዝ አሠራሩን ምቹና ቀልጣፋ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ተጠቃሽ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በዚህም መሠረት ባለፉት ሦስት ዓመታት 3 ሺህ 869 ብቻ የነበረው የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ቁጥር፣ በአሁኑ ወቅት በተከናወኑ አበረታች ሥራዎች ወደ 5 ሺህ 200 ማደጉን ኃላፊው ተናግረዋል።

ይህም ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ ለከተማዋ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።

በፎረሙ ላይ የተሳተፉትና በጨርቃጨርቅ ዘርፍ የተሰማሩት ባለሀብት አቶ ፍቃዱ ጉተማ እንደተናገሩት፤ መድረኩ መዘጋጀቱ ሥራቸውን ለማሳደግ ትልቅ እገዛ ይኖረዋል።

በአሁኑ ወቅት በመንግሥት የተፈጠረው ምቹ የሥራ ሁኔታ አበረታች በመሆኑ፣ ሠርቶ ለመለወጥ ከፍተኛ መነቃቃት እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል።

በፒፒሲ ፕላስቲክ ምርት ዘርፍ የተሰማሩት ወይዘሮ መጽሄት ከተማ በበኩላቸው፤ መንግሥት በፈጠረላቸው ምቹ ሁኔታ ወደ ሥራ በመግባታቸው ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን ጠቁመዋል።

በዚህም ከራሳቸው ባለፈ ለሌሎች ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻላቸውንና በከተማዋ ዕድገት ውስጥም የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026