የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ የገቢ አቅምን በማሳደግ ሁለንተናዊ ልማትን ለማፋጠን የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

Jul 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወላይታ ሶዶ፤ ሐምሌ 1/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የገቢ አቅምን በማሳደግ የክልሉን ሁለተናዊ ልማት ለማፋጠን የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ አስተዳደር አስታወቀ።

በወላይታ ሶዶ ከተማ የ2019 በጀት ዓመት የደረጃ "ለ" ግብር አሰባሰብ እና የንግድ ፈቃድ እድሳት ማስጀመሪያ ንቅናቄ ተካሂዷል።


በንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የኢኮኖሚ ዘርፍ አማካሪ አቶ ሳሙኤል ቀቀቦ እንዳሉት ግብር ለክልሉ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ስኬታማነት ጉልህ አስተዋጾ አለው።

ክልሉ ኢኮኖሚ የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ ከእርዳታ ጥገኝነት ከማላቀቅ ባለፈ የክልሉን ልማት በማፋጠን የህዝብን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ያግዛል ብለዋል።

በመሆኑም የክልሉን የገቢ አቅም በማሳደግ የክልሉን ሁለተናዊ ልማት ለማፋጠን የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።

ሁሉም ግብር ከፋይ ግብሩን በአግባቡና ታማኝነት ሲከፍል በገበያው ውስጥ ፍትሃዊና ጤናማ ውድድር ይፈጠራል ያሉት አማካሪው፣ ህገ ወጥ ንግድና የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን በቅንጅት ለመከላከል ይሰራል ብለዋል።


የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ እታገኝ ኃይለማሪያም በበኩላቸው ከተማ አስተዳደሩ የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ እና የከተማዋን እድገት ለማስቀጠል የውስጥ ገቢን አሟጥጦ ለመሰብሰብ ትኩረት መደረጉንም ገልጸዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የግብር ከፋዮን እንግልት ለማስቀረት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ታግዘው የሚሰሩ አምስት የግብር መክፈያ ማዕላትን ወደ ሥራ ለማስገባት መቻሉንም ጠቁመዋል፡፡


በግብር ዓመቱ በከተማው ካሉ ከ13 ሺህ 790 በላይ የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዮች ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ መታቀዱን የተናገሩት ደግሞ የወላይታ ሶዶ ከተማ ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ አማረች ዮሐንስ ናቸው።

ሁሉም የግብር መክፈያ ማዕከላት የቴሌ ብር ሲስተምን ጨምሮ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ከእጅ ንኪኪ ነፃ የሆነ አገልግሎት እንዲሰጡ ሙሉ ዝግጅት ተደርጎ ወደ ትግበራ መገባቱንም ጠቁመዋል።

ግብራቸውን በቴክኖሎጂ ታግዘው መክፈላቸው የጊዜና የጉልበት ብክነት እንዳስቀረላቸው የገለጹት ደግሞ አቶ አብርሃም ክፍሌ እና ወይዘሮ ትዝታ ደርጌ የተባሉ የከተማዋ ግብር ከፋዮች ናቸው።

ቀድመው መክፈላቸው በኋላ ይገጥማቸው ከነበረ የጊዜ ጥበት እንደሚታደጋቸው ገልጸው፣ ሌሎች ግብር ከፋዮችም ግብራቸውን በታማኝነት ቀድመው በመክፈል ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ መክረዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ትናንት በተካሄደ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት እንደሀገር በትሪሊዮን የሚቆጠር ገቢ እንደተገኘ መግለጻቸው ይታወሳል።

በግብር ዓመቱ ዲጂታል አሰራር መተግበሩና መደበኛ ካልሆኑ 43ሺህ የንግድ እንቅስቃሴዎች ግብር እንዲሰበሰብ መደረጉ ዘንድሮ የተገኘውን ገቢ ማሳደጉንም አመልክተዋል።

ክልሎችም በቀጣይ የገቢ አቅማቸውን በማጠናከር ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ የሚመደብ በጀትን ለታለመለት ዓላማ ማዋል እንዳለባቸው ማስገንዘባቸው የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች መሆኑን ...

Jul 9, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ምርታማነትን በማሻሻል የዘርፎችን ውጤታማነት አሳድጓል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተከተለችው የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ስኬታማ የሪፎርም ሥራዎች ምርታማነትን በማሳደግ የዘርፎችን ውጤታማነ...

Jul 9, 2026

የሕዝብን የልማት ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ ትኩረት ተሰጥቷል-አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)

ደሴ፤ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት የሕዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ በ...

Jul 7, 2026

በወላይታ ዞን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ

ወላይታ ሶዶ ፤ ሰኔ 24/2018(ኢዜአ)፦ በወላይታ ዞን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የግብር አሰባሰብ ሂደትን በመጠቀም ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የ...

Jul 3, 2026