የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ቀጣናዊ ግቦች እንዲሳኩ ከአባል ሀገራት ጋር በትብብር መስራቷን ታጠናክራለች

Jul 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ቀጣናዊ ግቦች እንዲሳኩ ከአባል ሀገራት ጋር በትብብር መስራቷን እንደምታጠናክር የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ።

የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር 22ኛው የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።


የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ገበያውን ወደ ሥራ ለማስገባትና የትስስሩን ተቋማዊ እድገት ለማስቀጠል ከፍተኛ ጥረት መደረጉን ጠቅሰዋል።

ትስስሩን ለመምራት ኢትዮጵያ በሊቀ-መንበርነት መመረጧን አስታውሰው፤ የተጀመሩ ቀጣናዊ ጥረቶችን ለማስቀጠል ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አረጋግጠዋል።

ኢትዮጵያ የትስስሩን በተቋማዊ ታማኝነት፣ በቀጣናዊ አንድነትና በሕግ የበላይነት ላይ የተመሰረተ የተቀናጀ ገበያ የመፍጠር የጋራ ግብን ለማሳካት ከሁሉም አባል ሀገራት ጋር ትብብሯን እንደምታጠናክር አመልክተዋል።

የጋራ ቁርጠኝነትን በማጉላት፣ ለአባል ሀገሮች ሁሉ ጥቅም ሲባል ድርጅታችንንም ሆነ ቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ገበያችንን ለማጠናከር የተገኘውን መልካም አጋጣሚ ልንጠቀምበት ይገባል ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል።


የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ደኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ ለጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ታንዛኒያ፣ ሱዳን ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ሚናዋን እየተወጣች ነው ብለዋል።

በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ማዕቀፍም ቀጣናውን በኃይል የማስተሳሰር ሚናዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል።

የምክር ቤቱ አስቸኳይ ስብሰባ በአባል ሀገራቱ መካከል በጋራ ለመስራት የተደረሱ ስምምነቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ አገልግሎት ውሎችን ጨምሮ በተለያዩ አሰራሮች ላይ ውይይት ተደርጎ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል።

በተጨማሪም የኤሌክትሪክ ገበያ ማዕከሉ ቦታ ለመወሰን ሌላው የጉባኤው ዋና የውይይት አጀንዳ መሆኑን ገልጸዋል።


የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር 13 ሀገራትን በአባልነት ያቀፈ ሲሆን፤ በአባል ሀገራቱ መካከል የኤሌክትሪክ ኃይልን በጋራ ለመጠቀም፣ የኃይል ግብይት ለማካሄድ እና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል ታልሞ የተመሠረተ ነው።

ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ታንዛንያ፣ ኡጋንዳ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ግብፅ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሩዋንዳ፣ ቡሩንዲ፣ ጅቡቲ፣ ሶማሊያና ሊቢያ የትስስሩ አባል ሀገራት ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች መሆኑን ...

Jul 9, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ምርታማነትን በማሻሻል የዘርፎችን ውጤታማነት አሳድጓል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተከተለችው የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ስኬታማ የሪፎርም ሥራዎች ምርታማነትን በማሳደግ የዘርፎችን ውጤታማነ...

Jul 9, 2026

የሕዝብን የልማት ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ ትኩረት ተሰጥቷል-አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)

ደሴ፤ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት የሕዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ በ...

Jul 7, 2026

በወላይታ ዞን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ

ወላይታ ሶዶ ፤ ሰኔ 24/2018(ኢዜአ)፦ በወላይታ ዞን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የግብር አሰባሰብ ሂደትን በመጠቀም ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የ...

Jul 3, 2026