🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ቀጣናዊ ግቦች እንዲሳኩ ከአባል ሀገራት ጋር በትብብር መስራቷን እንደምታጠናክር የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ።
የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር 22ኛው የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።

የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ገበያውን ወደ ሥራ ለማስገባትና የትስስሩን ተቋማዊ እድገት ለማስቀጠል ከፍተኛ ጥረት መደረጉን ጠቅሰዋል።
ትስስሩን ለመምራት ኢትዮጵያ በሊቀ-መንበርነት መመረጧን አስታውሰው፤ የተጀመሩ ቀጣናዊ ጥረቶችን ለማስቀጠል ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አረጋግጠዋል።
ኢትዮጵያ የትስስሩን በተቋማዊ ታማኝነት፣ በቀጣናዊ አንድነትና በሕግ የበላይነት ላይ የተመሰረተ የተቀናጀ ገበያ የመፍጠር የጋራ ግብን ለማሳካት ከሁሉም አባል ሀገራት ጋር ትብብሯን እንደምታጠናክር አመልክተዋል።
የጋራ ቁርጠኝነትን በማጉላት፣ ለአባል ሀገሮች ሁሉ ጥቅም ሲባል ድርጅታችንንም ሆነ ቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ገበያችንን ለማጠናከር የተገኘውን መልካም አጋጣሚ ልንጠቀምበት ይገባል ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ደኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ ለጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ታንዛኒያ፣ ሱዳን ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ሚናዋን እየተወጣች ነው ብለዋል።
በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ማዕቀፍም ቀጣናውን በኃይል የማስተሳሰር ሚናዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል።
የምክር ቤቱ አስቸኳይ ስብሰባ በአባል ሀገራቱ መካከል በጋራ ለመስራት የተደረሱ ስምምነቶች እንዲሁም የኤሌክትሪክ አገልግሎት ውሎችን ጨምሮ በተለያዩ አሰራሮች ላይ ውይይት ተደርጎ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል።
በተጨማሪም የኤሌክትሪክ ገበያ ማዕከሉ ቦታ ለመወሰን ሌላው የጉባኤው ዋና የውይይት አጀንዳ መሆኑን ገልጸዋል።

የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር 13 ሀገራትን በአባልነት ያቀፈ ሲሆን፤ በአባል ሀገራቱ መካከል የኤሌክትሪክ ኃይልን በጋራ ለመጠቀም፣ የኃይል ግብይት ለማካሄድ እና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል ታልሞ የተመሠረተ ነው።
ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ታንዛንያ፣ ኡጋንዳ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ግብፅ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሩዋንዳ፣ ቡሩንዲ፣ ጅቡቲ፣ ሶማሊያና ሊቢያ የትስስሩ አባል ሀገራት ናቸው።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች መሆኑን ...
Jul 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተከተለችው የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ስኬታማ የሪፎርም ሥራዎች ምርታማነትን በማሳደግ የዘርፎችን ውጤታማነ...
Jul 9, 2026
ደሴ፤ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት የሕዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ በ...
Jul 7, 2026
ወላይታ ሶዶ ፤ ሰኔ 24/2018(ኢዜአ)፦ በወላይታ ዞን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የግብር አሰባሰብ ሂደትን በመጠቀም ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የ...
Jul 3, 2026