🔇Unmute
ባህር ዳር ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሃብትን በጥናት በመለየት በተካሄደ የማልማት ተግባር ተጨባጭ ለውጥ መመዝገቡን የክልሉ ማዕድን ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የማዕድን ዘርፉ ተኪ ምርትና የውጭ ምንዛሬን ከማስገኘት ባለፈ የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ አይተኬ ኢኮኖሚያዊ ሚናውን እየተወጣ ይገኛል።
በቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዝናው አበበ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በክልሉ የሚገኘውን የማዕድን ሀብት በጥናትና ምርምር በመለየት ወደ ልማት እንዲገባ እየተደረገ ይገኛል።
በተለይም ባለፉት የለውጥ ዓመታት የማዕድን ዘርፉ በክልሉ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ውስጥ ሚናውን እንዲወጣ ለማድረግ የተሰራው ሥራ ተጨባጭ ለውጥ ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲዎችን በማሳተፍ የተፈጥሮ ጸጋን ለመለየት በተደረገው ሳይንሳዊ ጥናት በርካታ የማዕድን ሀብት በዓይነትም ሆነ በብዛት መኖሩ ተረጋግጧል ብለዋል።
በተለይም የወርቅና የግራናይት ማዕድናትን ጨምሮ የድንጋይ ከሰል፣ ኦፓል፣ ብረትና መሰል ማዕድናት በበቂ መጠን እንዳሉ በማረጋገጥ ወደ ልማት እንዲገቡ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
የማዕድን ዘርፉ ኢኮኖሚውን ከማነቃቃት ባሻገር፣ ከ73 ሺህ ለሚበልጡ ወገኖች የሥራ ዕድል በመፍጠር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለም አብራርተዋል።
ዘርፉን የበለጠ አጠናክሮ ለማስቀጠልም ለ198 ባለሀብቶች አዳዲስ የምርመራና የምርት ፈቃዶች ተሰጥተዋል።
እንዲሁም ለ2 ሺህ 835 ኢንተርፕራይዞች የባህላዊ እና ለ354 አነስተኛ የኮንስትራክሽን ድርጅቶች የማምረቻ ፈቃድ በመስጠት ወደ ሥራ እንዲገቡ መደረጉንም ጠቁመዋል።
በማዕድን ዘርፉ የተገኙ ተጨባጭ ውጤቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠልም የ25 ዓመት የልማትና የ5 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ወደ ትግበራ መግባቱን አክለው ገልጸዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026