🔇Unmute
አርባ ምንጭ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፡-የአርባ ምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መንግስታዊ አሰራርን በማቀናጀት ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ከማድረግ ባለፈ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን እንደፈታላቸው ተገልጋዮች ገለጹ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባ ምንጭ ክላስተር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች እንዳሉት የማዕከሉ ቀልጣፋ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት አስችሏል፡፡

ከተገልጋዮቹ መካከል ፓስፖርት ለማውጣት በማዕከሉ የተገኙት አቶ ገብረእግዚአብሔር ሃይለስላሴ በማዕከሉ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸው ጉዳያቸውን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመጨረስ አስችሏቸዋል።
ይህም ቀደም ሲል በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ሲስተዋል በነበረ መጓተት ይፈጠር የነበረውን የመልካም አስተዳደር ችግር መፍታት ችሏል ብለዋል።
የማዕከሉ ሠራተኞች አክብሮት የተሞላበት አገልግሎት እንደሰጧቸው ገልጸው፣ በማዕከሉ የተለያዩ አገልግሎቶች መስጠታቸው ጊዜ፣ ወጪና እንግልትን አስቀርቶልናል ብለዋል።
አገልግሎቱ በዲጂታል ሥርአት የታገዘ መሆኑ ቀልጣፋና ከሙስና የጸዳ አገልግሎት በፍትሀዊነት ለማግኘት እንዳስቻላቸው ገልጸዋል።

ዜጎችን ለምሬት ይዳርግ የነበረውን የመንግስት የአገልግሎት አሰጣጥ ያስተካከለው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የገለጹት ደግሞ ወይዘሮ ዘላለም አሸናፊ ናቸው።
የአገልግሎቱ ቀልጣፋና ውጤታማነት መንግስት አሰራሩን በማዘመን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል።
እሳቸውም የንግድ ፈቃዳቸውን ለማውጣት በመጡበት ወቅት ወደ ተለያዩ ተቋማት መሄድ ሳያስፈልጋቸው አገልግሎቶቹን ከመሶብ አገልግሎት ብቻ በተሟላ ሁኔታ ማግኘት መቻላቸውን ገልጸዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባ ምንጭ ክላስተር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስተባባሪ አቶ ይበቃል አሰፋ በበኩላቸው በማዕከሉ አምስት የክልልና አራት የፈደራል ተቋማት 32 አይነት አገልግሎቶች በዲጅታል ታግዘው እየተሰጡ መሆኑን አስረድተዋል።
ይህም ዜጎች ፍትሃዊ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ከእንግልት፣ ከእጅ መንሻና መሰል ችግሮች እንደታደጋቸው ገልጸዋል።
አሰራሩ መዘመኑ ስራን ከማቀላጠፍ ባለፈ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን በዘላቄታው ለመፍታት አስችሏል ብለዋል።
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026
አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...
Jul 24, 2026
ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...
Jul 16, 2026