የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በዞኖቹ የተተገበሩ አዳዲስ የግብርና ልማት ኢኒሼቲቮች የአርሶ አደሮችን ሕይወት በተጨባጭ እየቀየሩ ነው

Jul 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በኢሉ አባቦር እና ባሌ ዞኖች የተተገበሩ አዳዲስ የግብርና ልማት ኢኒሼቲቮች የወጣቶችንና የአርሶ አደሮችን ሕይወት በተጨባጭ እየቀየሩ መሆኑን የዞኖቹ አስተዳዳሪዎች ገለጹ።

በአዳማ አባ ገዳ አዳራሽ እየተካሄደ በሚገኘው የክልል መንግሥት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ላይ የተሳተፉ የዞን አስተዳዳሪዎች እንደተናገሩት ኢኒሼቲቮቹ በሁሉም መልኩ ስኬታማ እየሆኑ ነው።

የኢሉ አባቦር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ፤ ዞኑ ያለውን የተፈጥሮ ሀብት ወደ ዕድል በመቀየር በሁሉም ረገድ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ለውጥ እያመጡ ነው ብለዋል።

ዞኑ በተፈጥሮ ደን የበለጸገ መሆኑንና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ በተሰጠው ትኩረት በተከናወነው ሥራ የደን ሽፋኑ መጨመሩን ገልጸዋል።

ይህንን ያለውን አቅም ወደ ዕድል በመቀየር ረገድ በተከናወነው ሥራ የማር ልማት ኢኒሼቲቭ በሰፊው የተሰራበት መሆኑን ጠቅሰው ይህም በተለይ ወጣቶችን እና አርሶ አደሮችን የበለጠ ተጠቃሚ ማድረጉን ተናግረዋል።


በዚህም በየዓመቱ ዘመናዊ የንብ ማነቢያ ቀፎዎችን በማሰራጨት በዞኑ የማር ልማት በከፍተኛ ደረጃ እንዲስፋፋ መደረጉን አቶ እንዳልካቸው ገልጸዋል።

በማር ልማት ሥራ ላይ የተሰማሩ ወጣቶችና አርሶ አደሮችም የማር ምርታቸውን እስከ ውጭ አገር ገበያ ድረስ በማቅረብ ሕይወታቸውን እየቀየሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በዞኑ የሻይ ቅጠል ልማት ኢኒሼቲቭ ባለፉት ጥቂት ዓመታት አመቺ ሁኔታ ባላቸው ወረዳዎች ውስጥ እንዲስፋፋ በመደረጉ ኢኒሼቲቩ ለብዙዎች የሀብት ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል።

በባሌ ዞንም የግብርና ሥራን በሜካናይዜሽን በመደገፍ ምርታማነትን ለመጨመር የተከናወኑ አዳዲስ ኢኒሼቲቮች ውጤት ማምጣታቸውን የዞኑ አስተዳዳሪ ገልጸዋል።

በዚህም በዞኑ የግብርና ሥራን በሜካናይዜሽን በመደገፍ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር እየተከናወነ ባለው ሥራ ተጨባጭ ውጤት እየተገኘ መሆኑን የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ አብዱልሀኪም አሊይ ገልጸዋል።


በአሁኑ ወቅት በዞኑ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው የግብርና ሥራ በሜካናይዜሽን እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው በዓመት ከ800 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ተግባር ቀጥሏል ብለዋል።

በዞኑ በዓመት በክረምት፣ በበልግ ዝናብ እና በበጋ መስኖ ምርት እየተመረተ ሲሆን ይህም የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ ከመቀየር ባለፈ ተጠቃሚነትን እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል።

በተመሳሳይ በክልሉ ከተሞች የተተገበረውን የግብርና ኢኒሼቲቭ በመጠቀም የነዋሪውን ሕይወት ማሻሻል መቻሉን የተናገሩት ደግሞ የሞጆ ከተማ ከንቲባ አቶ ጋዛሊ ሀሹ ናቸው።

የከተማ ግብርና ኢኒሼቲቭ በተቀናጀ መንገድ ሥራ ላይ እየዋለ መሆኑን የገለጹት አቶ ጋዛሊ፤ የከተማዋ ነዋሪዎች የራሳቸውን ፍላጎት ከመሙላት አልፈው ምርታቸውን ለገበያ በማቅረብ ሕይወታቸውንና ኑሯቸውን እየቀየሩ መሆኑን አስረድተዋል።

የከተማ ግብርና በግለሰቦችና በተለያዩ ተቋማት ባዶ ቦታዎች ላይ በዘመናዊ መንገድ የተለያዩ ምርቶች እንዲመረቱ በማድረግ የምርት አቅርቦት እጥረትን እየቀረፈ መሆኑንም አንስተዋል።

ይህ የከተማ ግብርና ኢኒሼቲቭ ያሉትን ዕድሎች ሁሉ በመጠቀም እንዲለማ መደረጉ የከተማዋን ነዋሪ የሥራ ባህል ከመሠረቱ እየቀየረው መሆኑንና በርካታ ሥራ ፈላጊ ወጣቶችም ተደራጅተው በከተማ ግብርና ላይ በመሰማራት ኑሯቸውን ከመሠረቱ እየቀየሩ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች መሆኑን ...

Jul 9, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ምርታማነትን በማሻሻል የዘርፎችን ውጤታማነት አሳድጓል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተከተለችው የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ስኬታማ የሪፎርም ሥራዎች ምርታማነትን በማሳደግ የዘርፎችን ውጤታማነ...

Jul 9, 2026

የሕዝብን የልማት ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ ትኩረት ተሰጥቷል-አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)

ደሴ፤ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት የሕዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ በ...

Jul 7, 2026

በወላይታ ዞን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ

ወላይታ ሶዶ ፤ ሰኔ 24/2018(ኢዜአ)፦ በወላይታ ዞን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የግብር አሰባሰብ ሂደትን በመጠቀም ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የ...

Jul 3, 2026