የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በምሥራቅ ሸዋ ዞን የቡና ልማትን ለማላመድና ለማስፋፋት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

Jul 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን የቡና ልማትን ለማላመድና ለማስፋፋት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

የጽሕፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ አብነት ዘገየ ለኢዜአ እንዳስታወቁት፣ በክልሉ ከሚገኙ ዞኖች መካከል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ቀደም ሲል በቡና ልማት የማይታወቅ ነበር።


ይህንን ሁኔታ ለመቀየርም የዞኑ አስተዳደርና ግብርና ጽሕፈት ቤት በቁርጠኝነት እየሠሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

በዚህ ረገድ የመጣ የተሻሻለ የቡና ዝርያ በዞኑ በሚገኙ ሁለት የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች እየተዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰው፣ እስካሁንም 800 ሺህ የቡና ችግኞች ለተከላ መዘጋጀታቸውን አብራርተዋል።

የቡና ልማቱን በአጠቃላይ በግብርና ኢኒሼቲቭ መሠረት ለማስፋፋት ታቅዶ እየተሠራ መሆኑንም አቶ አብነት አመላክተዋል።

አዳማ፣ ሉሜ፣ ቦራ፣ አዳሚ ቱሉ፣ ዱግዳ እና መተሐራ አካባቢ በተመረጡ ቦታዎች የቡና ልማቱን ለማላመድና ለማስፋፋት ሰፊ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት በልማቱ የሚሳተፉ አርሶ አደሮች ልየታ ተደርጎ፣ የቡና ችግኝ መትከያ ጉድጓዶች በሳይንሳዊ ዘዴ በየደረጃው እየተዘጋጁ እንደሆነ ገልጸዋል።


በዚህም ለመጀመሪያ ጊዜ በዞኑ 200 ሄክታር አዲስ መሬት በቡና እንደሚሸፈን አመልክተዋል።

ከዚህ ቀደም የቡና ተክል በተበታተነ መልኩ ይተከል ከነበረበት አሠራር በመውጣት፣ በአዲስ ኢኒሼቲቭ በአንድ መንደር (በኩታገጠም) ለማልማት ታቅዶ በልዩ ትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

አካባቢው ለቡና ልማት ምቹ ሥነ-ምህዳር እንዳለው የጠቀሱት አቶ አብነት፣ አርሶ አደሮች ይህንን በመገንዘብ የቡና ልማትን ከሌሎች ሰብሎች ጎን ለጎን እንዲያካሂዱ ጥሪ አቅርበዋል።

ጽሕፈት ቤቱም የተሻሻሉ የቡና ችግኝ ዝርያዎችን ከማቅረብ ጀምሮ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026