የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ዩኒቨርሲቲው የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በምርጥ ዘር አቅርቦትና በእጽዋት በሽታ ቁጥጥር ላይ ሙያዊ ድጋፍ እያደረገ ነው

Jul 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሮቤ፤ ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፡- መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በምርጥ ዘር አቅርቦትና በእጽዋት በሽታ ቁጥጥር ላይ ሙያዊ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።

ዩኒቨርሲቲው በኩታገጠም አሰራር ለተደራጁ 120 አርሶ አደሮች የምርጥ ዘር ድጋፍ አድርጓል።

በመርሐግብሩ የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ፣ የምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት በዛብህ ወንድሙ (ዶ/ር) እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በምርጥ ዘርና በእጽዋት በሽታ ቁጥጥር ላይ እየሰራ ነው።


ለዚህም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በምርምር ያወጣቸውን የተሻሻሉ የስንዴ ዝርያዎችና የግብርና አሰራሮችን ለአርሶ አደሩ እያስተዋወቀ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ዩኒቨርሲቲው ከግብርና ምርምር ማዕከላት የተለቀቁ ምርጥ ዘሮችን በራሱና በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ በማባዛት ለአርሶ አደሩ መልሶ እያሰራጨ መሆኑንም አመልክተዋል።

ይህም የአርሶ አደሮች ምርታማነት ከአንድ ሄክታር እስከ 80 ኩንታል ስንዴ ማምረት እንዳስቻለ አንስተዋል።

ዩኒቨርሲቲው የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የጀመረውን ስራ በማስፋት ከባሌ፣ ምሥራቅ ባሌና ምዕራብ አርሲ በኩታገጠም ለሚሰሩ ለተመረጡ 240 ለሚበልጡ አርሶ አደሮች ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በዛሬው ዕለትም ከባሌ ዞን ለተመረጡ 120 አርሶ አደሮች የስንዴ ምርጥ ዘር ድጋፍ መደረጉ የጥረቱ አካልና ቀጣይነት ያለው መሆኑንም አመልክተዋል።

ዩኒቨርሲቲው አርሶ አደሩን በምርጥ ዘር አቅርቦትና ሌሎች የግብርና ድጋፎችን ከማድረግ በተጓዳኝ በእጽዋት በሽታ ቁጥጥር ላይ ተግባር ተኮር ሙያዊ ድጋፍ እየሰጠ መሆኑንም አመልክተዋል።


ድጋፉ ከተደረገላቸው አርሶ አደሮች መካከል ሐጅ ሁሴን አህመድ እንዳሉት በስንዴ ሰብል ልማት የመሳተፍ ረጅም ዓመት ልምድ ቢኖራቸውም ከምርጥ ዘር አጠቃቀም ልምድ ማነስ ምክንያት ከ25 ኩንታል የማይበልጥ የስንዴ እንደሚያመርቱ አስታውሰዋል።

በአሁኑ ወቅት ዩኒቨርሲቲው ያደረገላቸው የስንዴ ምርጥ ዘር ድጋፍ ምርታማነታቸውን ማሳደግ እንደሚያግዛቸው ገልጸዋል።


ዩኒቨርሲቲው ከምርጥ ዘር በተጓዳኝ በየጊዜው በሚያደርግላቸው ሙያዊ ድጋፍ ምርታማነታቸውን እንዳሳደገው የገለጹት ደግሞ ሌላው አርሶ አደር ሐጅ አማን ጎዳና ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026