የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በዞኑ ለመኸር እርሻ የሚውል ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ዘመናዊ የአፈር ማዳበሪያ እየተሰራጨ ነው

Jul 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ምስራቅ ጎጃም፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ)፡-በምስራቅ ጎጃም ዞን ለመኸር እርሻ የሚውል ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ዘመናዊ የአፈር ማዳበሪያ እየተሰራጨ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ምክትል ኃላፊ አቶ ጥላሁን ንጋቱ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በዘንድሮው ዓመት የመኸር ወቅት ማዳበሪያን ጨምሮ የተለያዮ ግብአቶች ጥቅም ላይ እንዲውሉ በማድረግ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል።

ለዚህም ከአንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ዞኑ በማስገባት የስርጭት ስራ መጀመሩን ነው የገለጹት።

ወደ ዞኑ ከገባው የአፈር ማዳበሪያ ውስጥም ከ980 ሺህ ኩንታል በላይ የሚሆነው ለአርሶ አደሩ ተደራሽ የተደረገ ሲሆን ቀሪው በስርጭት ላይ እንደሆነም ነው የገለጹት።

የማዳበሪያ አቅርቦቱ ምርታማነትን በማሳደግ ለኢንዱስትሪ ግብአትና ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት የራሱ የሆነ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አስገንዝበዋል።

በዞኑ የጎዛምን ወረዳ የጥጃን ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አያሌው ክፋሌ ፤ ለምርት ማሳደጊያ የሚሆን የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ መቅረቡ የዘር ስራችን በተገቢው መንገድ ለማከናወነ አስችሎናል ነው ያሉት።

በአሁኑ ወቅትም አራት ኩንታል የሚሆን የአፈር ማዳበሪያ በመውሰድም የበቆሎና ስንዴ ሰብል መዝራታቸውን አስረድተዋል።

የአነደድ ወረዳ የጉዳለማ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ላመስግን መለሰ በበኩላቸው፤የአፈር ማዳበሪያ ተጠቃሚ መሆናቸው ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚያግዛቸው ነው የተናገሩት።

የተረከቡትን ከአምስት ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ በመጠቀም መሬታቸውን በተለያዩ ሰብሎች ለመሸፈን እየሰሩ እንደሚገኙም አስረድተዋል።

በዞኑ በ2018/2019 የምርት ዘመን በዘር ከሚሸፈነው ማሳ ከ26 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ ተጠቁሟል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026