የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ የዜጎችን ጥያቄ የሚመልሱ የልማት ስራዎችን በመተግበር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል 

Jul 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቦንጋ ፤ሐምሌ 19/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የዜጎችን ጥያቄ የሚመልሱ የልማት ስራዎችን በመተግበር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለፁ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ በ85 ሚሊዮን ብር የተገነባው የኡማ ድልድይ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለፁት፣ የዜጎችን ጥያቄዎች የሚመልሱ ትልልቅ የልማት ስራዎችን በማቀድና ወደ ተግባር በመቀየር የማህበረሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው።


የክልሉ መንግስት ለፕሮጀክቱ ትኩረት በመስጠትና የነበሩ ችግሮችን በመፍታት በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ማስቻሉን ተናግረዋል።

ድልድዩ አርሶአደሩ በፍራፍሬ እና በእንስሳት ልማት እንዲሁም በእርሻ ስራ ላይ በሰፊው በመሰማራት የኢኮኖሚና ማህበራዊ እንቅስቃሴው ምቹ እንዲሆን ያስችላል ብለዋል፡፡

በሚከናወኑ የልማት ስራዎች የሕብረተሰቡ ተሳትፎ እያደገ የመጣ በመሆኑ ይህን አጠናክሮ በማስቀጠል የማህበረሰቡን ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችሉ ተግባራትም ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ፋጂዮ ሳፒ በበኩላቸው፤ ክልሉ ከተመሰረተ ወዲህ 20 የተለያየ ደረጃ ያላቸው ድልድዮች ተገንብተው ወደ ስራ መግባታቸውን አስታውሰዋል፡፡

ዛሬ የተመረቀው የኡማ ድልድይ ግን በርዝማኔው የመጀመሪያ መሆኑን ገልፀዋል።


ከሁለት ዓመት በፊት ግንባታው የተጀመረው የ84 ሜትር ርዝመት ያለው የኡማ ወንዝ ድልድይ ከ85 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበትም ተናግረዋል።

የኡማ ወንዝ ሞልቶ በርካታ የልማት ስራዎችንና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎችን ሲያስተጓጎል መቆየቱን የገለፁት ደግሞ የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ ናቸው።

አካባቢው ሰፊ የመልማት አቅም ያለው ነው ያሉት አቶ ታከለ፣ ድልድዩ ይህን ወደ ኢኮኖሚ በመቀየር፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን የሚያሳልጥ መሆኑን ተናግረዋል።

በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቅሬ አማንን ጨምሮ የክልል፣ የዞንና የወረዳው ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026