የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የአፍሪካ ሀገራት የልማት ግቦችን የሚያሳኩ የአሰራር ማዕቀፎችን በፍጥነት ወደ ስራ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል

Jul 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት አህጉራዊ የልማት ግቦችን እውን የሚያደርጉ ስምምነቶችን በአፋጣኝ አፅድቀው ወደ ትግበራ እንዲያስገቡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ጥሪ አቀረቡ።

49ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።


የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት አፍሪካ በመካከለኛው ምስራቅ ከቀጠለው ግጭት ጋር ተያይዞ የሚመጡ አሉታዊ ተፅዕኖዎችን በሙሉ አቅሟ እየተጋፈጠች ነው።

የግጭቱ መቀስቀስ የዓለም አቀፍ የአቅርቦት መስመሮችን በማስተጓጎሉ ምክንያት የነዳጅ፣ የሸቀጣሸቀጥ እና የመሰረታዊ ቁሳቁሶች ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሻቅብ ማድረጉን ገልጸዋል።

የአፍሪካ ህብረት ባለሙያዎች ጉዳዩን በጥልቀት ሲመረምሩት እንደቆዩና የዚህ ቀውስ ዳፋ ለበርካታ አመታት አብሮን ሊቆይ እንደሚችል ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን አብራርተዋል።

በሌላ በኩል በአህጉሪቱ እየተስፋፋ ያለው የሽብርተኝነት አደጋ እና የጤና ስጋት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ሊቀ መንበሩ አውስተዋል።

በሳህል ቀጣና ባደረጉት ጉብኝት የሰብአዊ ሁኔታዎችን መመልከትና ሽብርተኝነትን በጋራ መከላከል የሚያስችል ቀጣናዊ ትብብር ለማጠናከር ጥረት ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

የአፍሪካ የበሽታ መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከል (Africa CDC) እያከናወነ ላለው ስራ ላይ አባል ሀገራት ድጋፋቸውን እንዲያጠናከሩም ጠይቀዋል።

ሊቀ መንበሩ በአፍሪካ ህብረት የበጀት እና አደረጃጀት ላይ በሰጡት ማብራሪያም የ2027 የበጀት ረቂቅ 797 ሚሊየን 893 ሺህ 884 ዶላር መሆኑን ይፋ አድርገዋል።

ይህ በጀት ከአባል ሀገራት መደበኛ መዋጮ እና በዓለም አቀፍ አጋሮች የሚሸፈን መሆኑን ጠቁመዋል።

የአጀንዳ 2063 ሁለተኛውን የ10 ዓመት እቅድ ለማስፈጸም ወደ ሁለት ቢሊየን ዶላር ገደማ ፋይናንስ እንደሚያስፈልግ ነው ሊቀ መንበሩ ያስረዱት።

ኮሚሽኑ ለአፍሪካ ልማት የሚሆን የግል እና የህዝብ ካፒታልን መሳብ የሚያስችሉ ፖለቲካዊ እና ተቋማዊ ሁኔታዎችን የማመቻቸት ሚናውን እንደሚወጣም ተናግረዋል።

አባል ሀገራትም የህብረቱን የልማት ግቦች እውን ለማድረግ ቁልፍ የሆኑ ህጋዊ ስምምነቶችንና ሰነዶችን በፍጥነት እንዲያፀድቁ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026