የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

አፍሪካ አጀንዳዎቿን ለማስፈጸም የራሷን ሀብት መጠቀም ላይ ትኩረት ማድረግ አለባት

Jul 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018 (ኢዜአ)፦ አፍሪካ አጀንዳዎቿን ለማስፈጸምና ግቦቿን ለማሳካት የራሷን ሀብት መጠቀም ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባት የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ ኤድዋርድ ቢዚማና ገለጹ።

49ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

ስብሰባው እየተደረገ ያለው “ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ ነው።

የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት ሰብሳቢ ኤድዋርድ ቢዚማና አፍሪካ በጋራ ጉዳዮቿ ላይ በአንድ ድምፅና በተባበረ ክንድ መቆም እንዳለባት አስገንዝበዋል።

ሚኒስትሩ አፍሪካውያን ሁለንተናዊ ጥቅሟን ለማረጋገጥ በፓን-አፍሪካኒዝም እሴቶች ላይ የተመሠረተ ጠንካራ የጋራ አንድነት መገንባት አለባት ብለዋል።

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ማሻሻያ ላይ የአፍሪካ ሀገራት የጋራ አቋም የያዙባቸውና የህብረቱ ማዕቀፎች በሚገባ መተግበርና አፈጻጸማቸውን መከታተል እንደሚገባም አመልክተዋል።

ማዕቀፎቹ የአፍሪካን ፍላጎት በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስከበር ዋና መደላድል መሆናቸውን ነው የገለጹት።

የህብረቱን ዘላቂ የፋይናንስ ምንጭ በተመለከተ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ አፍሪካ የራሷን አጀንዳዎች ለማስፈጸምና በውሳኔ አሰጣጥ ላይ ነፃነቷን ለማስጠበቅ የራሷን ሀብት መጠቀም ላይ ትኩረት ማድረግ አለባት ብለዋል ሚኒስትሩ።

በዚህ ረገድም የአፍሪካ ሀገራት የፋይናንስ ድጋፋቸውን ማድረግ እንዳለባቸው ነው ጨምረው የተናገሩት።

ስምምነት እና መግባባት (Consensus) የፖለቲካ ብስለት እንጂ የድክመት ምልክት እንዳልሆነ ጠቁመው ይህም የአፍሪካ ሀገራትን የሚያቀራርቧቸውን የጋራ እሴቶች እንዲፈልጉ የሚያስችል ዋና መሳሪ ነው ብለዋል።

የተያዙ አጀንዳዎችንና የተገቡ ቃል ኪዳኖችን ለአፍሪካውያን ህይወት ለውጥ ወደሚያመጡ ተጨባጭ ውጤቶች መቀየር እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026